Wednesday, July 20, 2011

“አን ዱ” የለም እንጂ “አን ዱ” ማ ቢኖር?

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብዙ ብዙ ፈተናወችን አልፋ እዚህ ለመድረሷ ጥርጥር የሌለው ሀቅ ነው በዘመናችን ያለው ፈተና ግን ስትራቴጂዎች በመቀየስ እስከ አሁን ካለው ኑፋቄያዊ አስተምሮ በተለየ መልኩ ቤተ ክርስቲያኗን ባለችበት ከእነ ምእመኗ እና ሕንፃዋ ሙሉ በሙሉ ፕሮቴስታንታዊ አድርጎ መውረስ የስልቱ የመጨረሻ ግቦች ነው የተለመዱ የተሐድሶ ስትራቴጂዎች፡ ‹‹አባቶችን መከፋፈል እና የአንዱ ደጋፊ የሌላው ነቃፊ መምሰል፣ የጥላቻ ጽሑፎችን በማሰራጨት ምእመናንን ማደናገር፣ ፖለቲካዊ ክሶችን ማቅረብ፣ ከገዳማት እናቶችን ማስኮብለል፣ የነጋዴዎች እና የብፁዓን አበው ደጋፊ መስሎ መቅረብ፣ ብዙ ውስጠ ወይራ የሆኑ የጽዋ ማኅበራትን መመሥረት፣ ጉባኤያትን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ እንዲካሄዱ እገዛ ማድረግ፣ በተቻለ መጠን የውስጥ ለውስጥ(Underground) ሥራዎችን በይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል(ለዚህም ከገድላት የተወሰኑ መቀበል)፣ የፎርጅድ ጽላት ዝግጅት፣ የሙዳየ ምጽዋት ብርበራ፣ የቤተ ክርስቲያን ቃጠሎ እና ንዋየ ቅድሳት ዘረፋ፣ የቤተ ክርስቲያንን ሕንጻ በግለሰብ ስም ማዛወር፤ የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ አባል በመሆን፣ በከተሞች ታላላቅ ጉባኤያትን በማዘጋጀት በገዳማት እና አድባራት ስም ገንዘብ ማሰባሰብ እና ለግል ጥቅም ማዋል፣ ፎርጅድ ማኅተሞችን በማዘጋጀት በአባቶች ስም ልመና ማካሄድ፣ በባሕታዊነት ስም መነገድ እና አስነዋሪ ድርጊቶችን በአደባባይ እና ሰዉ በሚያይባቸው ቦታዎች በመፈጸም ሕዝቡ ባሕታዊ እና መነኩሴ እንዲጠላ ማድረግ፣ ገዳማት ውስጥ እየገቡ በተለያዩ ሰንካላ ሰበቦች ሁከት መፍጠር እና ጠብ አስነሥቶ የተወሰኑትን አስወጥቶ ይዞ በመጥፋት እነዚያን የመናፍቃን ሰለባ ማድረግ፣ ገዳማትንም መፍታት›› ምን አለ “ አን ዱ“ ቢኖር ይህን ኩሉ ጉድ ለመፈፀም የተዘጋጁትንና እየሄዱበት ያለውን አቅጣጫ ሁሉ አንድ ወደ ኋላ ብለንው የአባቶቻችንን አሰተምሮ እንዲሰብኩ ፎረማት ባረግናቸው ነበር ፡፡
“አን ዱ” ያው እንደምታውቁት በኮምፒውተር አጠቃቀም ለይ የ “አን ዱ” ጥቅም የማይረዳ የለምና አንድ ነገር ስንሳሳት የ “አን ዱ” ኮማንድ በመጠቀም የነበረውን እንዳልነበረ የደርገዋል ታዲያ ይሄ “አን ዱ” የሚባል ነገር እንደ ኮምፒውተር በኑራችንም ቢኖር ምናለበት ታዲያ ይህን አንዱ ተጠቅመን ኑፋቄውን እነዳለነበር ያለፉትን አበው ለእምነት ለተዋህዶ የቆሙትን እነደ ቅዱስ ቄርሎስ ያሉትን መልሰናቸው “ሥላሴ አትበሉ” ለሚሉት ለእነበጋሻው አይነቱ ይህን ምስጢረ ሥላሴን ከ ሀ ጀምረው ያስረዱት ነበር እንዲህም ብለው ምስጢረ ስላሴን “እግዚአብሄር በአካል ሶስት በባህርይ አንድ ብለን እናምናለን፡፡ይሄውም ፦ አንድ መለኮት ፣ አንድ ባህርይ ፣ አንድ ልእልና ፣ አንድ ጌትነት ፣ አንድ ክብር ፣ ከጥንት አስቀድሞ የነበረ አንድ ቀዳማዊነት ነው ፤ ደግሞም በሶስት አካላት ፣ በ ሶስት ገፃት ፍፁማን ናቸው ፣ ግዙፋን አይደሉም ፣ ያልተፈጠሩ ናቸው ፣ ድካም የማይስማማቸው የማይለወጡ ናቸው ፣ ለመገኘት ጥንት ለዘመን ፍፃሜ የላቸውም፡፡ ወልደ እግዚአብሄር ዳግመኛም ከአብ ባህርይ የተገኘ አምላክ ፣ ቃል ፣ ወልድ ፣ ያልተፈጠረ ፣በመለኮት አንድ ከሚሆኑ ከሶስቱ አካላት አንድ አካል ፣ ከአብ ጋር ትክክል የሚሆን ፣ አለም ሳይፈጠር በመለኮታዊ ልደቱ ከአብ የተወለደ ፣ ፍፁም እግዚአብሄር አብን በመልክ የሚመስለው ፣ በባህርይ የሚተካከለው የማይመረመረ የጌትነቱ መታወቂያ እንደሆነ እናምናለን፡፡ በገፁ በአካሉ ልዩ የሚሆን የአብ ልጅ ፣ አምላክ ፣ ቃል በአባቱ ፈቃድ ፣ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ለእኛ ቤዛ ሆኖ ተሰጠ፡፡ ያልተፈጠረ ፣ ስጋ ያልነበረው ፣ የማይለወጥ እርሱ እግዚአብሄር ቃል በማይመረመር ግብር በመልኩ ፣ በአምሳሉ የፈጠረንን እኛን ሰወችን ለማዳን ከአብ አንድነት ሳይለይ ከሰማይ ወረደ፡፡ ቃል ስጋ መሆን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ሲሆን ሰው ሆነ ፤ ከጌትነቱ ክብር ፈፅሞ አልተለየም ፤ ምንም ሰው ቢሆን እርሱ ከፍጡራን ሁሉ በላይ ነው ፤ በመለኮቱ ህግን የሰራ ሲሆን እነሆ ህግን በመፈፅም ተገኘ ፤ ህግን ሲሰጥ በነበረበት ባህርይውም ፀንቶ ኖረ፡፡ በመለኮቱ ገዢ ሲሆን የተገዢ ባህርይን ገንዘብ አደረገ ፣ ግን የጌትነት ክብር ከእርሱ አልተለየም ፤ አንድ ሲሆን ለብዙወቹ ምእመናን በኩር ሆነ ፤ በአንድነቱም ፀንቶ ኖረ፡፡ በማይመረመር ምስጢር እንደ እኛ በመሃፀን መፀነስን ወደደ ፤ እርሱ ሰው እንደመሆኑ በመሃፀን ሳለ በባህርይ መለኮቱ በሰማይ በምድር ፣ ከምድርም በታች ምሉእ ነው ፤ በማይመረመር በማይነገር ጌትነቱም በአብ እሪና ይኖር ነበረ ፤ የሕይወት እስትንፋስ ያላቸው ሁሉ በላይ በታች ያሉ ፍጡራንም ሁሉ በመሃል እጁ ናቸው ፤ አሽናፊ ፈጣሪ እርሱ እንደ ከሃሊነቱ ሁሉን ያዝዛቸዋል፡፡ መለኮትና ትስብእት በተመለከተ እግዚአብሄር ወልድ በድንግል መሀፀን ሳለ በሰማይም በምድርም ከአባቱ ጋር አንድ ባህርይ መለኮት ህልው ነውና ከሃጢአት በቀር በመሀፀን ሆኖ ከተፈጠረ ከፍፁም ትስብእት ጋርም በማይመረመር ባንድ ባህርይ መለኮት መቸም መች አንድ ነውና፡፡ እግዚአብሄር አብን በመልክ የሚመስለው ፣ በባህርይ የሚስተካከለው እርሱ ቀምቶ እግዚአብሄር የሆነ አይደለም ራሱን አዋርዶ የተገዥን ባህርይን ገንዘብ አደረገ እንጂ ፤ መለኮትስ እንደሰው በድንግል መሀፀን ያለ የእለት ፅንስ በመሆን በድንግል ማህፀን ሳለ በሰማይ በምድር ምሉ ነው፡፡ ደግሞ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በጥቂት በጥቂት ማደጉን ወንጌላውያን ፃፉልን ፦ በየጥቂቱ ያደገ ግን መለኮት አይደለም ፡ በሰማይም በምድርም የመላ ነውና ፤ በሁሉ በሰማይ በምድር የመላው እንዴት ያድጋል? ከተዋሃደው ስጋ ጋር አንድ አካል አንድ ባህርይ ነውና በየጥቂቱ ማደግን ገንዘብ አደረገ፡፡ ከሃጢአት ብቻ በቀር እንደ እኛ በስራው ሁሉ ተፈተነ ፣ ተራበ ፣ ተጠማ ፣ ደከመ ፣ አንቀላፋ ፣ በላ ፣ ጠጣ ፣ አለቀሰ ፣ ተከዘ ፣ አዘነ ፣ ታመመ ፣ ሞተ ፣ ተገነዘ ፣ በመቃብርም ተቀበረ ፤ ይህስ እንዴት ለመለኮት ይነገራል? ነገር ግን እግዚአብሄር ቃል በተዋሃደው ስጋ ስለእኛ ይህን ሁሉ ገንዘብ አደረገ፡፡ መለኮት ግን ከመከራ ሁሉ የራቀ ነው፡፡ (ወይንስ) በባህር ላይ ተራመደ ፣ ሙታንን አስነሳ ፣ ድውያንን ፈወሰ ፣ ከሞት ተነሳ ፣ በዝግ ቤት ገባ ፣ ወደ ሰማይ አረገ እንደምን ይባላል? ይህ የትስብእት ገንዘቧ አይደለምና ፣ ነገር ግን ሰውን ሰለመውደዱ የቃል ገንዘብ ለትስብእት ሆነ እንጂ ፤ እኛም ሰው አምላክ ሆነ ስለዚህ እንላለን፡፡ እንግዲህስ እግዚአብሄር ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋው ሞተ እንላለን እንጂ በባህርይው (በመለኮቱ) ከሞተስ እነሆ አብም ሞተ ደግሞ እንላለን ፣ እነሆ መንፈስ ቅዱስ ሞተ ደግሞ እንላለን ፤ ነገር ግን መለኮት ህማም ሞት ስለሌለበት እግዚአብሄር ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋው ሞተ እንላለን፡፡
አበው ባስረዱት ነበር ምን ያረጋል ታዲያ “አን ዱ“ በህይወታችን የለም እነጂ የቄርሎስ ትምህርቱ እንዲህ እንየው ታዲያ አልዛርን ከሞት ያስነሳው ማን ነው? ወይንስ እግዚአብሄር የሚለው ስም ከሶስቱ አካላት የማን ነው? እናንተ አልዛርን ከሞት ያስነሳው ኢየሱስ ነው እግዚአብሄር አይደለም የምትል እስኪ መልስልኝ ፦ ይህ ስም የአብ ብቻ ነውን? አባቶች እንዳስተማሩን ይህስ የሶስቱም የአንድነት ስማቸው ነው፡፡ እኛም እግዚአብሄር ስንል ፦ እግዚአብሄር አብ ፣ እግዚአብሄር ወልድ ፣እግዚአብሄር መንፈስ ቅዱስ ማለታችን እንደሆነ እናውቃለን፡፡ እስኪ መልሱልኝ ፦ አልዛርን ከሞት ያስነሳው ኢየሱስ ብቻ ነው የምትሉ መለኮትን ትከፍሉት ዘንድስ ማን አስተማራችሁ? ወይንስ ለስላሴ ስንት መለኮት አለው? ስላሴ ግን በባህርይው አንድ መለኮት እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ወይንስ ኢየሱስ ክርስቶስ አልዛርን ከሞት ያስነሳው በቃል ገንዘብ ነውን? ወይንስ በትስብእት ገንዘብ? ይህንስ የኢየሱስ ክርስቶስን ባህርይ ትከፍሉ እንደሆነ ጠየቅኳችሁ፤ ነገር ግን እግዚአብሄር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ በተዋህዶ አንድ እንደሆነ እኛ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች እናምናለን፡፡ እንግዲህ የቃል ገንዘብ ለትስብእት እንደሆነ በመለኮቱ ሰማይና ምድርን የመላ ፣ በስልጣኑ ሁሉን የፈጠረ እርሱ በመለኮቱ ስልጣን አልአዛርን ከሞት አስነሳው እንላለን ፤ የስላሴ መለኮትም አንድ ነውና ስላሴ ደግሞ አልአዛርን ከሞት አስነሳው እንላለን ፣ ይህም መለኮት የእግዚአብሄር አብ ነውና እግዚአብሄር አብ አልአዛርን ከሞት አስነሳው ደግሞ እንላለን፤ ለመንፈስ ቅዱስም ይህ ይነገር ዘንድ ይሆናል፡፡ መለኮት ከ ትስብእት ለአይን ጥቅሻ እንኳን እንዳልተለየው ፦ አንድ በሆነው መለኮት አብም መንፈስ ቅዱስም ወልድን በስራው ሁሉ አልተለዩትም ፤ እግዚአብሄር ወልድም ምንም ስጋን በመልበሱ በምድር ቢሆን በመለኮቱ ግን ከዙፋኑ አልተለየም፡፡እንዲህ ስንል ግን እግዚአብሄር አብ ሞተ እንላለንን? ወይንስ እግዚአብሄር መንፈስ ቅዱስ ተሰቀለ እንላለን? እስኪ መልሱልኝ መለኮት ይሞታልን? ይሰቀላልን? አይሞትም አይሰቀልምም ፤ ስለዚህም እግዚአብሄር አብ ፣ እግዚአብሄር መንፈስ ቅዱስ ፣ ወይንም ስላሴ ሞቱ አንልም፤ ነገር ግን እግዚአብሄር ወልድ በተዋሃደው ስጋ ስለእኛ ይህን ሁሉ ገንዘብ አደረገ ብለን እናምናለን ፡፡ እንግዲህስ ይህን አባቶች አስተማሩን ፤ እናንተ ግን አዲስን ትምህርት ከየት አመጣችሁት? እኛ ግን አልአዛርን ባስነሳው እግዚአብሄር እናምናለን፡፡ አበው ባስረዱት ነበር ምን ያረጋል ታዲያ “አን ዱ“ የለም እንጂ “አን ዱ“ ቢኖር እንደ በጋሻው ያለውን መምህር አበው አቃንተውት ልጁንም ፎርማት ባደረጉት ነበር፡፡
ያንን ወንድሞች በቅንነት እውነተኛ መስሎአቸው እናገለግልበታለን ብለው የገቡበትን ‹‹የቅድስት ማርያም የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ማኅበርም እነ በጋሻውና የሬድ አደመ ባልፈጠሩት ነበር ‹‹የቅድስት ማርያም የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ማኅበር›› - ይህ ማኅበር በቅርብ ጊዜ የተቋቋመ(እነ በጋሻው ደሳለኝ እና ያሬድ አደመ በዋናነት የሚሳተፉበት) ሲሆን የተቋቋመባቸው ዋና ዋና ዓላማዎች፡- (1)የትምህርት አሰጣጡን ይዘት ከመሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ይልቅ ግራና ቀኝ ወደማያስለይ እና መሠረታዊ ቁም ነገር ወደማያስጨብጥ ተራ ወግ እና ተረት መለወጥ ነው፤ የዚህ ተግባር ዓላማም ምእመኑ መሠረታዊ የሆነውን የቤተ ክርስቲያኑን አስተምህሮ እንዳያውቅና እንዲህ ከሆነም የሚጫንበትን ኑፋቄ ሳያቅማማ እና ሳይለይ እንዲቀበል ለማድረግ ነው፡፡ (2)የስብከተ ወንጌሉን አቅጣጫ ለቤተ ክርስቲያናችን ወካይ ዓርማ (Icon) የሚባሉትን ነገሮች የሚያጥላላ እና የሚያናንቅ ማድረግ ነው፡፡ በዚህም ሕዝቡ ለቤተ ክርስቲያን ያለውን አክብሮት እንዲቀንስ እና እንዲጥል ከዚያም በውስጡ ቤተ ክርስቲያኑን እንዲጠላ ማድረግ ነው፡፡ (3)ሃይማኖታዊ ልዩነቶችን ማጥፋት፤ ይህም ፕሮቴስታንታዊውን አስተምህሮ አሾልኮ በማስገባት ‹‹አንድ ነን፣ እዚህም እዚያም የሚሰበከው ጌታ ነው፤. . . ወዘተ›› በማለት ከውስጥ ሆኖ መለወጥ ነው፡፡ (4)የተለያዩ ማኅበራትን በሕዋስ(Cell) ደረጃ በየጉራንጉሩ መመሥረት እና ማቋቋም፤ እነዚህን ጥቃቅን ማኅበራት አህጉረ ስብከት ስለማያውቋቸው እና የሚቆጣጠሩበትም መንገድ ስለ ሌላቸው እነዚህ የሚያዘጋጇቸው ጉባኤያት፣ የሚጋብዟቸው ሰባክያን እና በዚያም የሚሰጠው ትምህርት ለዓላማቸው የተመቸ ይሆናል፤ እየሆነም ነው፡፡ (5) በስብከቶቻቸው እና በጽሑፎቻቸው የፕሮቴስታንቶችን ምንጮች መጠቀም፣ ለዚህም በቅርብ ጊዜ ያሳተሙት መጥሐፍ ሐሳቡ ብቻ ሳይሆን ርእሱ ሳይቀር የፕሮቴስታንት ፓስተር ከጻፈው መጽሐፍ የተወሰደ ነው፡፡ ታዲያ “አን ዱ “ በህየወታችን ቢኖር ኖሮ ሰለስቱ ምዕት አቕጣጫውን በእነሱ መስመር ባቃኑት ነበር ትምህርት ጤፉ በጋሻው ይህን ወደ መሰለው የ”እኔ ከሞትሁ ሠርዶ አይብቀል” ግዙፍ ድምዳሜ ለመድረስ በንጽጽሩ ምን ያህል ቦታዎችን በመነሻነት እንደወሰደ አይታወቅም፡፡ የሚታወቅ ነገር ቢኖር መምህረ ሃይማኖት ባሕታዊ ኀይለ ጊዮርጊስ የተባሉ ሰባኬ ወንጌል እንደተናገሩት፣ በጋሻው እና “የሞንታርቦ ወንድሞቹ” ትውልዱ ማንነቱን ለይቶ በማያውቅበት የምሽት ጉባኤዎች ድብልቅልቅ በማደንዘዝ ሀብቱን እየበዘበዙ፣ እናት ቤተ ክርስቲያኑን በፕሮቴስታንታዊ-ተሐድሶ-ኑፋቄ አዳክሞ ለመውረስ አልያም ከፍሎ ለመረከብ ላሰፈሰፉ ኀይሎች በሎሌነት እያገለገሉ መሆናቸው ነው፡፡ ታዲያ ይባስ ብለው ሰዎች በአውደ ምህረትህ ላይ ለፀሎት ተሰብስበው በ "እግዚኦ መሃርነ ክርስቶስ" አንተን በሚማፀኑበት ወቅትም፥ ፍፁም በሚያውክና በእልህ በተሞላ ድምፅ መዝሙር ለመባል ስርዓት በጎደለው ጩኧት ቤትህን አመሱት። አማኙንም ከአምልኮ ስርዓቱ ለማስተጓጎልና ቤትህ በመታደስና በመፅዳት ላይ መሆኑን የሚያሳይ ምሳሌ ለማኖር አፀድህን በሚቃጠል ቆሻሻ ጢስ አጠኑት። “አን ዱ “ ቢኖር ኖሮ! በሰጠሀቸው ፀጋ በፊትህ ተመፃደቁ፤ ትምክህታቸውም ፈር ለቀቀና በሀሰት ትምህርታቸው ህዝብህን አደናገሩት። በመንደር ወሬና ስድብ አስመርረውም አስለቀሱት። በገዛ ደምህ የዋጀሀትን ቤተ ክርስቲያን ‘አርጅታለች’ አሉና ለእድሳቱ ሚስማርና መዶሻ ለመዋዋስ ከመናፍቃን ጋር መከሩ። አረጀች ያሏትን ቤተክርስቲያንም በሣራ መሰሏት፤ እነሱም በስተርጅና የተወለዱ የሣራ ልጆች መሆናቸውን አበሰሩን። “አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ፥ በጽቅድቅ ጨለማ መብራቱ ይጠፋል።” (መጽሐፈ ምሳሌ 20:20) የሚለውን የወንጌል ቃል ስተውት ይሁን ንቀውት፥ በ40 እና በ80 ቀን የእግዚአብሄር ልጅነትን ያገኙና ቤተክርስቲያንን ያውቁ ዘንድ እንኳን ያልከለከሉዋቸውንና፥ ሀገርንና ሀይማኖትን ከጠላት ጠብቀው ያቆዩላቸውን አባቶች "የእንጨት ሽበቶች፣ ፍንዳታዎች" ብለው ለቀለለ ስድብ አፋቸውን ከፈቱ መንፈስ እንዳዘዘን እናስተምራለን” ከሚል “የዘመኑ ሐዋርያ ነኝ” ባይ ምእመኑ ምን ይማራል? “ንጉሣችን ቅልጥ አድርጎ ይዘምራል፤ አባባ ሲተኛ እኛ እንነቃለን፣ እኛ ስንተኛ እርሱ ይሠራል፤ ሥላሴ ሲያጫውቱ ያሥቃሉ፣ እሺ፤ በጣም ነው የሚያጫውቱት፤ ተባበሩኝ ብለው የሚያሥቁ ኮሜዲያን አሉ፤ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ እንደዛ አይደሉም፤ ለማርያም ከበሮ አይመታም ለጌታ እንጂ፤ ከጸበሉ ይልቅ የሚያጽናናቸው ቃሉ ብቻ ነው፤ በአንድ ወቅት በራስ ቅል ኮረብታ ላይ ኢየሱስ እና ዲያቢሎስ ቁማር ተጫወቱ…ዲያቢሎስም በጨበጣ ገባ፤ እኛ ሕዝቡን ጨፍረን እናምጣው፣ እናንተ መዝሙር አስተምሩት፤ እኛ ሕዝቡን ደንሰን እናምጣው፤ እናንተ ሥርዐት አስተምሩት፤ እኛ ሕዝቡን ጨፍረን እናምጣው እናንተ ሃይማኖት አስተምሩት፤ ይሄ ሕዝብ እኛ ሳንወድቅ ወድቋል፤ እኛ የምናምነው በፈውስ፣ በዝማሬ በጸጋ ነው፤ ‹በተሰጠኝ ጸጋ ሰይጣን ፎቶዬን ሲያይ መጮህ ጀምሯል› [ጋሞጎፋ ሳውላ ኪዳነ ምሕረት]” የሚል ሰባኪ ነኝ ባይ ዋልጌ የግል ተክለ ሰብእናውን ከመገንባት ውጭ እንደምን ምእመኑን በሃይማኖቱ ለማጽናት ይቻለዋል? ታዲያ ምን ያረጋል በዚህ ሁሉ ነገር “አን ዱ” ቢኖር ኖሮ አበውም በመጡ ታሀድሶም በጠፋ ነበር አምላክ ሆይ በጎችህ በተኩላዎች እንዳይነጠቁብህም የተኩላዎቹን አፍ ዝጋ፤ የበጎችህንም ንቃት አብዛ። የአሳቾቹም የጨለማ ጉዞ “እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው።” (ወደ ሮሜ ሰዎች 1:28) እንደሚለው ያንተው ፈቃድ ከሆነም፤ እባክህ ስለቅዱሳን ብለህ የዚህችን ቤተክርስቲያን ጥፋት አታሳየን ልቦናቸውንም አብርተህ ዳግም አንተን ያውቁ ዘንድ ይሁን።

No comments:

Post a Comment