Friday, April 15, 2022




ሁሌም ቢሆን ስርዓተ ቤተ ክርስቲያን ሲጣስ እያየን ዝም የሚል ልብ የለንም፡፡ በተለይ በመድረክ አገልግሎት ላይ በመናያቸው ስርዓተ ቤተ ክርስቲያን ሲጣስ ማየተ ደግሞ በጣሙን የቆስላል፡፡ መቼም ሳይገባው የቤተ ክርስቲያን መድረክ ላይ ለመውጣት የሚደፍር አለ ብለን አናስብም ትንሽም ቢሆን ሚስጠራትን የተማረ እና የስርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ያወቀ ይሆናል ተብሎ ይገመታል፡፡ እንደ ቤተ ክርስቲያናችን ስርዓትማ ካየንው አንድ ሰው ወደ አገልግሎት ከመግባቱ በፊት በፈሪሐ እግዚአብሔርለቅረብ መወሰን በአምላክህ በእግዚአብሔር ፊት መልካምና ቅን የሆነውን ነገር ስታደርግ ለአንተ ከአንተም በኋላ ለልጆችህ ለዘላለም መልካም ይሆንላችሁ ዘንድ እኔ የማዝዝህን እነዚህን ቃሎች ሁሉ ሰምተህ ጠብቅ። ዘዳ.12:28፤ እንደተባልንው ስንመላለስ  እግዚአብሔርን በመፍራት መሆን ይኖርብናል  እግዚአብሔርን የሚፈራ ትውልድ ደግሞ ለእግዚአብሔር ቃል ይገዛል  በእግዚአብሔርም የባረካል፡፡ በንስሃ ህይወቱም ሁል ጊዜ ተጠብቆ መኖርም ይገባል እንግዲህ እንዴት እንደ ተቀበልህና እንደ ሰማህ አስብ፥ ጠብቀውም ንስሐም ግባ ራእ.3:3 ንስሃ የሚገባ ሰው ደግሞ ህይወቱ በፀሎት የመሰረታል ሁል ጊዜም ይሰግዳል ይጾማልም ለአገልግሎቱም መቃናተ ፈቃደ እግዚአብሔርን በመጠየቅ ይሆናል፡፡ እነኝህ ያነሳናቸው በጣም ጥቂቱን ግዴታዎች ነው  ይህቺን ትንሻን ህይወት የሌለው ክርስቲያን አገልጋይ አይደለም ክርስቲያን ለመሆኑም ጥርጣሬ ውስጥ ይገባል፡፡
ይሁንና ይህቺን በጥቂቱ ያልነው  የዘማሪት ዘርፌ አይን ያወጣ ጋብቻ ነው፡፡ ዘማሪት ዘርፌ ከበደ ማናት በዘፋኝነት  ህይወት እያለች ምን አይነት ህይወት ነበራት የሚሉትን ሁሉ እንተወውና በቤተ ክርስቲያናችን ወደ አገልግሎት ከመጣች ብኋላ በኢትዮጵያ እያለች ከፕሮትስታንት ተሃድሶ አራማጆች ጎን ብዙ ጊዜ ስሟ ሲነሳ የነበረ ሲሆን ወደ አሜሪካም ከሄደች ወዲህ ከአባ ወልደተነሳይ ጋር በአንድ ጉባኤ ለአገልግሎት እንደምትሳተፍ መረጃዎች ያስረዳሉ፡፡ ዘማሪት ዘርፌ በኢትዮጵያም እያለች ከጋምቤላ ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ  ረዳት የሆነውን ዲ/ን አይናለምን ከጋምቤላ ከተማው ውጪ በለ አድባር በቅዱስ ቁርባን ማግባቷ ለማንም የተደበቀ አይደለም፡፡ ከዚየም ወደ አዲስ አበባም ሲመጣ አብረው እንደነበሩም የሚታወቅ ሲሆን ከኢትዮጵያ ከወጣች ብኋላ ደግሞ በአሜሪካ ሎሳንጀለስ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ እሰጢፋኖስ የነበረው ዲ/ን ዘገብርኤል ጋራ በስርዓተ ተክሊል ሁለተኛዋን ጋብቻ ፈፅማለች፡፡ መጀመሪያ በስርዓተ ቁርባን ሁለተኛውን ደግሞ በስርዓተ ተክሊል ልብ በሉ በቤተ ክርስቲያናችን  ስርዓት ጋብቻ ሲፈፀም ከቤተ ክርስቲያን ከወጣ ብኋላ ምን አይነት አለባበስ  የኖረዋል የሚለውን ለእናንተ ትተን ስርዓተ ተክሊል በቤተ ክርስቲያን ስርዓት መስረት እንዴት ይፈፀማል የሚለውን ጥቂት እንመልከት፡፡
በሚታየው አገልግሎት የማይታየውን ፀጋ ከምናገኝባቸው ውስጥ ከሰባቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን አንዱ የማይደገም  ምስጢረ ተክሊል ነው ፡፡    ምስጢረ ተክሊል የሚፈፀመው በፍትሃ ነገስት አንቀፅ 24፡ 906 ላይ እንደተገለጣ የመጀመሪያው ሥጋው ድንግልና ነው ፡፡  ከሁለት ተጋቢዎች አንዱ ድንግልናውን ያጣ እንደሆን በድንግልና ላለው ስርአተ ተክሊሉ ተፈፅሞለት ተክሊል የሚያደርግ ሲሆን ድንግል ላልሆነው ግን ፀሎተ ንስሃ ተነቦለት ቅዱስ ቁርባኑን ተቀብለው ጋብቻቸው ይፈፀማል ፡፡
ልላው ድንግልናቸውን በተለያዩ ምክነያቶች ላጡ ለምሳሌ በሕክምና የተነሳ፤ በተፈጥሮ ሲወለዱ የድንግልና ምልክት የሌላቸው፤ ለአቅመ ሔዋን ሳይደርሱ ተገደው የተደፈሩ፤ ከአቅም በላይ የሆነ ስራ በመስራት ድንግላናቸውን ያጡ ስርዓተ ተክሊል ሊፈፀምላቸው ይችላል፡፡ ይህ በዚሁ እንዳለ ስርአተ ተክሊል የሚፈፀመው የሃየማኖት አንድነት ላላቸው 2ኛ ቆሮ. 6፡ 14-18፤ ፍቃደኝነታቸውን ለገለፁ ተጋቢዎች እና ከ 20 አመት እድሜ በላይ  ለወንዱ ፡ከ15 እድሜ ኣመት በላይ ለሴት ከሆኑ እንድሆነ ሰረዓተ ተክሊል ይፈፀምላቸዋል፡፡ ይህንንማ ፍትሐ ነገስት አንቀፅ 24 ፤883-884፤894 እና 906 ላይ በስፋት ተዘርዝሯል፡፡
በድንግልና ለመኖር ወስኖ ቃልኪዳኑን ትቶ አፍርሶ ያለ አንድ ሰው ፀሎተ ተክሊል ሳይፈፀምለጽ በቁርባን ብቻ ማግባት  የተፈቀደ ነው፡፡ ፍትሐ ነገስት አንቀፅ 24፤ 834 ሰው ለእግዚአብሔር ስእለት ቢሳል፥ ወይም ራሱ በመሐላ ቢያስር፥ ቃሉን አይስበር፤ ከአፉ እንደ ወጣው ሁሉ ያድርግ ሴትም ደግሞ ለእግዚአብሔር ስእለት ብትሳል፥ እርስዋም በአባትዋ ቤት ሳለች በብላቴንነትዋ ጊዜ ራስዋን በመሐላ ብታስር አባትዋም ራስዋን ያሰረችበትን መሐላ ስእለትዋንም ቢሰማ፥ አባትዋም ዝም ቢላት፥ ስእለትዋ ሁሉ ይጸናል፥ ራስዋንም ያሰረችበት መሐላ ሁሉ ይጸናል።ዘኊ.30:2፤
በስዓርተ ተክሊል ተጋብተው ባል ወይም ሚስት አንዱ የሞተ እንድሆን እና በሕይወት ያለው ለማግባት ቢፈልግ ግን ሚስቱ የሞተችበት  ከአንድ ዓመት ብኋላ፤ ባሏ የሞተባት ከ10 ወር ብኋላ ከሐዘናቸው ተፅናንታ ማግባት ይችላሉ ይህም በፍትሐ ነገስት አንቀፅ24 ፤ 916 ተገልጧል፡፡
በጥቂቱ  ስለ ስርዓተ ተክሊል ካየን  ዘማሪት ዘርፌን ከላይ ከጠቀስንው የሚገልፃት የቱ ነው፡፡
1.    በጋብቻ ላይ ጋብቻ መፈፀሟ
2.    ከበፊቱ ባሏ ወደ ልላ ካህን ባል ማግባቷ
3.    የቤተ ክርስቲያንን ስርዓት በአደባባይ መጣሷ እና ማስጠሷ
4.    አርአያ በመሆን ፋንታ ብጣሽ ጨርቅ ለብሶ ገላን እያሳዩ ከበሮ መምታቷ
5.    ማህተብ ሳታስር መታየቷ
ሌላም ሌላም ሌላም ብቻ ሁሉም ስርአተ ቤተ ክርስቲያን ለምን አልተከበረም ዋናው ጥያቄ ነው ለአንድ አገልጋይ ነኝ ባይ ደግሞ ይህቺን ጥቂቷን የቤተ ክርስቲያን ግዴታ መወጣት ግዴታው ነው ባዮች ነን፡፡ የእኛ ድርሻመሆን ያለበት እንዲህ መሰሉን ኢሰርአተ ቤተ ክርስቲያን ሲፈፀም ተመልክተን ማለፍ ሳይሆን እንዳይደግም የራሳችንን ጥረት ማድረግ የጠበቅብናል፡፡

ለቤተ ክርስቲያናችን ስርዓት መከበር ያለሰለሰ ጥረት እናድርግ ፡፡
ይህን እንድናደርግ እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

                                                                                                          

ፓትርያርክ ምርጫ እስከ ሚከናወን ድረስ ከዐቃቤ መንበረ ፓትርያርኩና ከቋሚ ሲኖዶስ ጋር አብረው የሚሠሩት አባላት በእርቀ ሰላሙ ጉዳይ ከአቡነ መርቆሬዎስ ጋር ተወያዩ

ከጥቅምት 6-11 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ሠላሳ አንደኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ይካሔዳል፡፡ 
የጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋናው ስባሰባ ደግሞ ጥቅምት 12  እንደሚጀመር እየተጠበቀ ሲሆን በአሁን ሰዓት እንዱና አንገብጋቢው አጀንዳ የፓትርያርክ ምርጫ እና ተያያዥ ጉዳዮች እንደሚሆን እየተጠበቀ ነው ፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከውጪው ሲኖዶስ ጋር ያለውን እርቀ ሰላ በተመለከተ ከዚህ በፊት እንደሚታወቀው አቡነ መልከፄዴቅ ጋር ብቻ ውይይት ሲደረግ የቆየ ቢሆንም ሰሞኑን የዋናው ፓትርያርክ ምርጫ እስከ ሚከናወን ድረስ ከዐቃቤ መንበረ ፓትርያርኩና ከቋሚ ሲኖዶስ ጋር አብረው የሚሠሩ ሰባ አባላት    ከአቡነ መርቆሬዎስ ጋር ወይይት ማድረጋቸው ተነግሯል ፡፡

በውይይቱም አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ በፊት እንደሚገመተው ሁሉ በገዳም መኖርን እንደሚመርጡና አንድ  ጊዜ የተጣሰው ስርዓት እሳቸው በህይወት እያሉ ሌላ ፓትርያርክ እንዲመረጥ እንደማይፈቅዱና እሳችው እስኪያርፉ አሁን እንዳለው ቤተ ክርስቲያኗ በመንበረ ፓትርያርክ እየተመራች እንድትቆይ እንደሚሹ ማስታወቃቸውን ምንጮቻችን ዘግበውልናል፡፡
ልዑል እግዚአብሔር የቤተ ክርስቲያናችንን አንድነት ይጠብቅልን፡፡
ቸር ወሬ ያሰማን፤  አሜን፡፡

†ወበዛቲ ዕለት አዕረፈ ቅዱስ አቡነ ሲኖዳ†



በስመ ሥላሴ
ወበዛቲ ዕለት አዕረፈ ቅዱስ አቡነ ሲኖዳ መርህ ለመንግስተ ሰማያት”
“ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅመ እግዚአብሔር” (የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።) መዝ.፻፲፭፡፲፭ (115፡15)
እግዚአብሔር ያፈቅሮሙ ለጻድቃን እግዚአብሔር የዐቅቦሙ ለፈላስያን፡፡ (እግዚአብሔር ጻድቃንን ይወድዳል፤ እግዚአብሔር  ስደተኞችን ይጠብቃል፡፡)“ መዝ.፻፵፭፡፰ (145፡8)
አቡነ ሲኖዳ የተባሉት አንዳንድ ፀሒፍያን ሀገራቸው ሸዋ ነው ይላል። ሀገራቸው ግን ጎጀም ደብረ ጽሞና ምስራቅ ከተባለው አሁን ገዳማቸው ከሚገኝበት ቦታ ተወለዱ። በ፲፬ኛ መቶ ክፍለ ዘመን በአፄ ይስሐቅ ጊዜ የነበሩ ጻድቅ ናቸው። በዚህ በጎጀም በደብረ ጽሞና የነበሩት ሕዝቦች በዘንዶ ያመልኩ ነበርና ያንን የሚያመልኩትን ዘንዶ በመስቀላቸው ሲባርኩ ከሁለት ተሰንጥቆ ሞቷል። የሀገሩንም ሕዝብ አስተምረው አጥምቀው ቤተ ክርስቲያን በእመቤታችን ስም ሰርተው ሰጥተዋቸዋል። እነሱም “ሲኖዳ ቅዱስ አቡነ መርህ ለመንግስተ ሰማያት” ብለዋቸዋል። በዚህም ጌታችን አስደናቂ ቃል ኪዳን ሰጥቶአቸዋል።