Monday, March 26, 2012

የለገዳዲ የቅ/ኪዳነ ምህረት ተአምር




የካቲት 16/2004 ዓ.ም  የቃል ኪዳኗ ታቦት ለእመቤታችን ቃል ኪዳን በተገባበት ቀን ለማክበር  ከህናት ወደ ዋሻው ገብተው ታቦቷን ተሸክመው ወደ  ድንኳን መጡ፡፡ እልልታው ቀለጠ ግማሹ በደስታ የለቅሳል ቀድሞ የፈረሰው የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን  ጋር የተጣለው ድንኳን ደረሱ ታቦት ተሸካሚው ካህን ምልክት አሳዩ ታቦትን መሸከም አልቻልኩም አቃጠለኝ ካህን ይቀየርልኝ አሉ፡፡ በሌላ ካህን ተቀየሩ ሕዝቡም እንዲረጋጋ ተነገረው፡፡ ወረብ ስብከት ወደፊት ለሚሰራው መቃኞ ቤተ ክርስቲያን እርዳታ ተሰበሰበ ስርዓት ቅዳሴ በድንኳን ውስጥ ተከነወነ፡፡ ከዚያም ታቦተ ቅድስት ኪዳነምህረትን ይዘው ከድንኳን ጉዞ ተጀመረ፡፡ ለወንጌል መስፋፋት ዘወትር የሚደክሙት ደከመኝ ሰለቸኝ የማይሉት የለገዳዲ ወጣቶች ቀይ ቲሸርት ለብሰው ቀይ ምንጣፍ የሚያነጥፉ ተቦቷን ወደ መጣችበት ዋሻ ለመመለስ ይዘምራሉ፡፡ ድንገት ድምፅ ተሰማ አልቅሱ ምዕመናን አልቅሱ እግዚአብሔር እንዲታረቀን አልቅሱ የሚል  በሞንታርቦ ድምጽ ተሰማ  ምዕመናን ሁሉ ተደናገጡ ታቦተ ኪዳነ ምህረትን የተሸከሙትን ሁለኛው ካህን እያለቀሱ ድምጽ አሰሙ፡፡ ተቃጠልኩ አንሱልኝ አልቻኩም እግዚኦ በሉ ብለው በወደቁበት ይጮኃሉ ግን ማን ታቦቷን ያንሳላቸው፡፡ እሳትን ማን ይደፍራል፡፡ ጩኽቱ ምህላው ለቅሶው እግዚኦታው ቀጠለ ግን ማንም ታቦቷን ማንሳት አልቻለም ሕዝበ ክርስቲያን እንደ ሻሽ ተነጥፈው አለቀሱ መነኮሳት እና ካህናት አነቡ በብዙ ለቅሶና እግዚኦታ ቆሞሱ አባታችን በወደቁበት ቦታ ሆነው ወደ ዋሻ አትመልሱኝ ክብሬ መገለጫው ደርሷል ወደ ድንኳን አስገቡኝ ብላለች ሲሉ በቀላሉ ብድግ አለችና ወደ ድንኳን ገባች፡፡ ሁለተኛው ታቦት ተሸካሚው ካህን ከወደቁበት ለማንሳት ተሞከረ እራሳቸውን ስተው በሕይወትና በሞት መካከል ሳሉ ወጣቶች ካህኑን ከካህን ጋር ይዘው ወደ ፀበሉ ሮጡ ታቦት ተሸካሚው ካህን ሲጠመቁ በእሳት የጋለ ብረት ምጣድ ውሃ ሲፈስበት የሚያወጣውን ድምጽ እና ጭስ እሰቸውም ላይ ታየ ከብዙ ሰዓታት ቆይተ በኋላ እራሳቸውን አወቁ፡፡ ካህናቱ የወደቁት ኃጢያተኛ ስለሆኑ ሳይሆን የቅድስት ኪዳነ ምህረት ዕለት ወደ ዋሻ አልገባም ብላ በተዓምቷ ቦታውን ስአስከበረች ነው፡፡ የወረዳው ምክር ቤት ፍልፍል ቤተክስቲያን ኃይማኖታዊ እና ታሪከዊ ቦታነቱን የታቦቷን ሃያልነት አምነው ተቀበሉ፡፡ ግን ቦታውን እስካሁን ለቤተክስቲያኗ አልሰጡም  ጠንካራው  የለገዳዲ ምዕመናን ግን በጥቂት ቀን ውስጥ መቃኞ ቤተክስቲያን ስርቶ አጠናቆ እሁድ መጋቢት 16/2004 ዓ.ም ፅላቷን ከድንኳን ወደ መቃኞ በሰላም ገብታለች ሕዝበ ክርስቲያኑም ከተለያየ ቦታ እየመጡ እየተፈወሱ ናቸው  በቀጣይ የተሸለ ቤተ ክርስቲያን ሰርቶ በቅርብ ማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ሁላችንም የራሳችንን ድርሻ እንድንወጣ ይገባል መልክታችን ነው ፡፡
አምላክ ቤተክርስቲያናችንን ከጠላት ይጠብቅልን


Tuesday, March 20, 2012

የዋልድባ ጉዳይ አበቃለት ማለት ነው?

እንዴት ነው ነገሩ የዋልድባ ጉዳይ አበቃለት ማለት ነው? ትላንት መንግስት ስምምነት ላይ እንደተደረሰ እና ሌላ ሀሳብ ያለው ካለ ግን ብሎ  “ገዳማችን ይህን የሚደግፍ እንጂ የፀረ ሰላም ሀይሎች መሸሸጊያ አይደለም በዋልድባ ገዳም ስም የግል ጥቅማቸውን ለማራመድ የሚሯሯጡ ኃይሎችን እንቃወማለን” በማለት ፓለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ማድረጉ ምን ይሉታል እውን ወደ 18 አብያተ ክርስቲያናትን መንግስት እንዲያፈርስ መነኮሳቱ የሚፈቅዱ የመስለናልን? ይልቁንም ለመሰዋት እንደተዘጋጁ ባለፈው ሳምንት ሐሙስ በ6/7/04  በቪኦዬ ሪዲዮ የቀረበውን እንስማ


Monday, March 19, 2012

የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ዛሬም በደኑ ላይ የእሳት ቃጠሎው በንፋስ ሀይል በጣም እየተባባሰ ነው

የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ዛሬም   በደኑ ላይየእሳት ቃጠሎው በንፋስ ሀይል በጣም እየተባባሰ ነው በአሁን ሰዓትም ከፍተኛ እርዳታ እንደሚፈልጉ ገልፀውልናል ቃጠሎው ትላንት ቅዳሜ 08/07/04 እንደጀመረ ለማወቅ ተችሎአል በአሞራ ገደል(የመላእክት ከተማ) አካባቢ መሆኑ እሳቱን ለማጥፋት ከባደ አድርጎታል
 

መንግሥት ከአካባቢው የውኃ ቦቴዎችን እና ወታደሮችን በማንቀሳቀስ ውኃውን ለማጥፋት ጥረት እያደረገ ቢሆንም እሳቱ ግን ወደ ገዳሙ በመጠጋት ላይ ነው፡፡
አሁን አማራጫችን አንድ ብቻ ነው፡፡ የዝቋላን ገዳም ከማጣታችን በፊት ያለንን ነገር ሁሉ ይዘን በተገኘው ትራንስፖርት ወደ ዝቋላ መትመም ብቻ፡፡ ወንበር ማርያም ድረስ የውኃ ቦቴዎቹ ሊደርሱ ይችላሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ያለውን ባገኘነው ዕቃ ሁሉ ውኃውን ይዘን በመውጣት መረባረብ፡፡ ያለበለዚያ ግን የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ወደ ታሪክነት ይቀየራል፡፡
እነሆ ክርስትናችን የሚፈተንበት፣ ኢትዮጵያዊነታችንም የሚለካበት ጊዜ መጣ፣ በእሳት ተቃጥለው ያቆዩትን ገዳም ከእሳት ማዳን ካልቻልን እንግዲህ የኛ መኖር ትርጉሙ ምንድን ነው?
 

Sunday, March 18, 2012

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ 3ኛ አረፉ

ደጉን መምህር አውነተኛውን አባት ታታሪዉን ወንጌላዊ ንጹውን መነኮስ አጣናቸው



የቤተ ክርስቲያኗ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትና የቅዱስ ማርቆስ መንበር 117ኛ ፓትርያርክ የቅዱስነታቸው ዕረፍት የታወቀው ትናንት መጋቢት 8 ቀን 2004 ዓ.ም. ነበር፡፡ በሰሜናዊ ግብፅ፣ አስዩት ውስጥ ሐምሌ 27 ቀን 1915 ዓ.ም ሲወለዱ ቅዱስነታቸው በካንሰር ሕመም ምክንያት በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል
 
ታላቅ አባት ቤተ ክርስቲያናችን አጣች አምላክ ነፍሳቸውን በገነት የሳርፍልን
 


Thursday, March 1, 2012

አገልግሎት


አገልግሎት  በዲ/ን ዳንኤል ክብረት

ኤር.48:10 የእግዚአብሔርን ሥራ በቸልታ የሚያደግ ርጉም ይሁን፥ ሰይፉንም ከደም የሚከለክል ርጉም ይሁን