Monday, March 19, 2012

የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ዛሬም በደኑ ላይ የእሳት ቃጠሎው በንፋስ ሀይል በጣም እየተባባሰ ነው

የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ዛሬም   በደኑ ላይየእሳት ቃጠሎው በንፋስ ሀይል በጣም እየተባባሰ ነው በአሁን ሰዓትም ከፍተኛ እርዳታ እንደሚፈልጉ ገልፀውልናል ቃጠሎው ትላንት ቅዳሜ 08/07/04 እንደጀመረ ለማወቅ ተችሎአል በአሞራ ገደል(የመላእክት ከተማ) አካባቢ መሆኑ እሳቱን ለማጥፋት ከባደ አድርጎታል
 

መንግሥት ከአካባቢው የውኃ ቦቴዎችን እና ወታደሮችን በማንቀሳቀስ ውኃውን ለማጥፋት ጥረት እያደረገ ቢሆንም እሳቱ ግን ወደ ገዳሙ በመጠጋት ላይ ነው፡፡
አሁን አማራጫችን አንድ ብቻ ነው፡፡ የዝቋላን ገዳም ከማጣታችን በፊት ያለንን ነገር ሁሉ ይዘን በተገኘው ትራንስፖርት ወደ ዝቋላ መትመም ብቻ፡፡ ወንበር ማርያም ድረስ የውኃ ቦቴዎቹ ሊደርሱ ይችላሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ያለውን ባገኘነው ዕቃ ሁሉ ውኃውን ይዘን በመውጣት መረባረብ፡፡ ያለበለዚያ ግን የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ወደ ታሪክነት ይቀየራል፡፡
እነሆ ክርስትናችን የሚፈተንበት፣ ኢትዮጵያዊነታችንም የሚለካበት ጊዜ መጣ፣ በእሳት ተቃጥለው ያቆዩትን ገዳም ከእሳት ማዳን ካልቻልን እንግዲህ የኛ መኖር ትርጉሙ ምንድን ነው?
 

No comments:

Post a Comment