Thursday, June 23, 2011

እውን ‹‹ተሐድሶ›› የለምን?

ሰሞኑን በተደጋጋሚ ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም ማኅበረ ቅዱሳን የፈጠረው ወሬ ነው!›› የሚል ንግግር በመስማቴ ይህንን አጭር ማሳሰቢያ ለመጻፍ ተነሳሣው፡፡ በእርግ...ጥ ንግግሩን ቀደም ሲልም ሰምቼው አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን መደጋገሙ ሲበዛ በተለይም ግምት የሰጠዋቸው ሰዎች ነገሩን ተቀብለዉት ስመለከት ለካ የሚናቅ ሐሰት የለም አሰኘኝ! ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን የፈጠረው ወሬ ነው!›› ለሚለው ለምን ፈጠረው? ይህን ሐሳብ ፈጥሮ ምን ይጠቀማል? ቢፈጥረውስ እናንተ ተሐድሶ ካልሆናችሁ ምናችሁ ይነካል?  የሚል የራሴን ጥያቄ ፈጥሮ ከመጠየቅ በቀር እኔን ስለማይመለከተኝ የማኅበሩ የቤት ሥራ ነውና ራሱ ይጨነቅበት ብዬ አልፌዋለሁ፡፡ ትንሽ ማብራሪያ ለመስጠት የምሞክረው ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም›› በሚለው አመለካከት ላይ ነው፡፡ በእርግጥ አንድን ነገር እያለ ‹‹የለም›› ማለት አንድም ሐሰት ዳግመኛም የጥፋት ስልት መሆኑ ይታወቃል፡፡ የአጥፊዎች ሁሉ አውራ የሆነ ሰይጣንም ይህን ስልት በተለያየ መንገድ ሲጠቀምበት ይታያል፡፡ ሰይጣን በሰዎች ልቡና ያድርና ራሱን ደብቆ ክፉ ሥራ ሲያሠራቸው ይኖራል፡፡ በወንጌል እንደተነገረው በጾም፣ በጸሎትና በመንፈሳዊ ሥራ እንዲሁም በተቀደሰ ውሃና አፈር (በጸበል) ኃይሉ ሲደክምበት ‹‹ተቃጠልኩ›› እያለ ይለፈልፋል፡፡ በዚህ ጊዜ ሰይጣን መሆኑ ታውቆ አስፈላጊውን መንፈሳዊ ሥርዓት በማከናወን ያንን ሰው ለቆ እንዲወጣ ይገሠጻል፤ ይረገማል፤ ይገዘታል፡፡ ወዲያውም ለቆ ይሄዳል፡፡ ክርስቲያኖች ይህን የሰይጣን ክፋትና አሠራር ያውቃሉ፡፡ ይሁን እንጂ በእግዚአብሔር መኖር የማያምኑ ከሃዲዎች በሰይጣን መኖርም አያምኑም፡፡ ሰይጣን እነዚህን ሰዎች እኔ ‹‹የለውም›› እያለ ይዘብትባቸዋል፤ ይዋሻቸዋል፡፡ እነርሱም በጸበል ሲለፈልፍ አይተው በሥራህ ተገለጥክ፤ አወቅንብህ እንዳይሉት እንኳን ይህ እኮ ጭንቀት ነው፤ ቅዠት ነው፤ ኢሉዥን ነው /illusion/፤ ኮንፍዩዥን ነው /Confusion/ ወዘተ እያለ ምክንያት በመደርደር አለመኖሩን ሊያሳምናቸው ይጥራል፡፡ በዚህም ሐሳቡን የተቀበሉት በርካቶች ናቸው፡፡ ይገርማል! ሥራው እየታየ፤ ንግግሩ እየተሰማ የለውም ማለቱ አቤት የሰይጣን ድርቅና! የተሐድሶ አራማጆች ሥራ ዓይኑን አፍጥቶ ጥርሱን አግጥጦ በሚታይበት በዚህ ዘመን ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የፈጠራ ወሬ ነው እንጂ በእውን ያለ ነገር አይደለም›› ማለት አንድም አይኔን ግንባር ያድርገው ከማለት ይቆጠራል፡፡ ወይም ደግሞ ከላይ በምሳሌ እንደተጠቀሰው አቅጣጫ የማስቀየር የቅሰጣ ተግባር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ሌላው ቢቀር ፊደል የለየና ማንበብ የሚችል ሰው ከአንድ አሥር ዓመት ወዲህ የወጡትን በተመሳሳይ ርእሰ ጉዳዮች የተጻፉትን የሕትመት ውጤቶች ከሁሉም አቅጣጫ ቢከታተል ‹‹ተሐድሶ›› በቀናች ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ዶግማ ቀኖና እና ትውፊት ላይ ያነጣጠረ በጥናት የተቀነባበረ የጥፋት ስልት እንጂ  ጭራቅን የመሰለ የፈጠራ ወሬ አለመሆኑን በቀላሉ ይረዳል፡፡ ‹‹ተሐድሶዎች›› ራሳቸው የቁርጥ ቀን መድረሱን እያወጁ ወደ አደባባይ ሲመች በቃልና በጽሑፍ ሳይመች ደግሞ በጉልበት ጭምር እየተጋፉ ለመውጣት በሚሽቀዳደሙበት በዚህ ጊዜ ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር›› የለም ማለት ከ‹‹ተሐድሶነት›› የከፋ የሐሰት ምስክርነት ነው፡፡ በአገራችን የከተማና የገጠር ጎዳናዎች ላይ ሲመላለስ ‹‹…የተሐድሶ ቤተ ክርስቲያን›› የሚል ጽሑፍ እያነበበ ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም›› የሚል ሰው ምን ሊባል ይችላል? የማያውቅ ሰው የዚህኛው ከዛኛው ልዩነቱ ምንድር ነው? አንድ ናቸውን? እያለ ይጠይቃል እንጂ በማያውቀው ነገር ደፍሮ ምስክርነት አይሰጥም፡፡ በዛሬ ጊዜ ‹‹ተሐድሶአዊ እንቅስቃሴ የለም›› ማለት በሚቃጠል ቤት ውስጥ ጭስ አፍኖት እየሳለ በር ዘግቶ እንደመቀመጥ ይቆጠራል፡፡ ዛፍ በፍሬው እንደሚታወቅ ‹‹የተሐድሶ እንቅስቃሴም›› መገለጫዎች አሉት፡፡ እነዚያን እየመረመሩ ‹‹እንግድዳ ትምህርት›› (ዕብ13.9) ሲያገኙ መለየት እንጂ ‹‹ተሐድሶ የት አለ?›› ‹‹ተሐድሶዎቹስ እነማን ናቸው?›› የሚል ዓይነት ያልበሰለ አጠያየቅ ከእውነታው እንድንርቅ ሊያደርገን ይችላል፡፡ በየመንፈሳዊ መድረኮች ላይ ሁለት ዓይነት ልሣን ማድመጥ እየተለመደ መጥቷል፡፡ የቱ ‹‹እንግዳ ትምህርት›› እንደሆነ የእረኛቸውን ድምፅ የሚሰሙ እውነተኛ በጎች ለይተው ያውቁታል፡፡ የሴት ድምፅ ከወንድ እንደሚለይ ልዩነቱ ጉልህ ነውና፡፡ ዕረፍት የማይሰጡ፤ የቃላት ድርደራዎችና ጩኽቶች ከማሳመን እና ጥያቄን ከመመለስ ይልቅ ሌላ ጥያቄ የሚያጭሩ፣ የሚያጠራጥሩና የሚያስጨንቁ ስብከቶችና ‹‹መዝሙሮች›› የምን ነጸብራቅ ናቸው? ከአንድ የተሰወረ ምንጭ ካልቀዱትስ በቀር ብዙ ሰዎች አንድ ዓይነት ዘይቤ፣ ቃላት፣ ድምፅና እንቅስቃሴ ሊኖራቸው እንዴት ይችላል? በዚሁም ላይ ይህ ሁሉ ደግሞ ከመናፍቃኑ ጋር አንድ መሆኑ ምን ይጠቁማል? ‹‹ከተሐድሶ›› ስልቶች አንዱ በስውር መንቀሳቀስ ነው፡፡ ይህ በጥናትና በዓላማ የሚተገበር በመሆኑ በማስተዋል ካልሆነ በፍጥነት ለመለየት ያስቸግር ይሆናል፡፡ ይሁን እንጂ የአንድን ተክል ምንነት ለይቶ ለማወቅ ቅጠሉንና ፍሬውን ማየት ብቻ በቂ ነው፡፡ ለዚህም ገበሬ መሆን አይጠይቅም፡፡ ይህ ኮክ ነው፤ ይህ ወይን ነው፤ ይህ በለስ ነው! ለማለት ቆፍሮ ሥሩን የሚያይ የለም፡፡ ሥሩ በምክንያት ከመሬት ውስጥ መቀበሩ ይታወቃልና፡፡ ሥሩ ምንም ይሁን ምን የተክሉን ዓይነት ለይቶ ለማወቅ ቅጠሉንና ፍሬውን ማየት ብቻ በቂ ነው፡፡ እንደዚሁም የ‹‹ተሐድሶ እንቅስቃሴ›› መራራ ፍሬው በስሎ አዝመራውም ነጥቶ እየታየ ነውና ልብ ያለው ልብ ይበል! ‹‹ተሐድሶ የሚባል የለም›› እያሉ ስለማያውቁት ነገር ምስክርነት ከመስጠት፤ ለጥፋትም ሥራ ተባባሪ ከመሆን፤ ራስንና ሌሎችንም ከመጉዳት የሚቀድመው አፍን መሰብሰብና ራስን መመርመር ነው፡፡ ‹‹የተሐድሶ›› ሴራ ስውር እንደመሆኑ መጠን የዚህ የጨለማ ሥራ ሰለባ ከሆኑና ያላመኑበት ጉዳይ ከሆነ ይህንንም እውነት ዘግይተው ከተረዱ የሚሻለው ቶሎ መመለስ ነው፡፡ ‹‹ተሐድሶ የሚባል የለም›› ማለት ራስን የሚያድን መንገድ ስላልሆነ ከወዲሁ ንስሐ መግባት ይገባል፡፡ እንዲያውም ሌሎች እንዳይጠፉ መረጃ መስጠትና ካገኙት ልምድ በማካፈል አካሄድን ማሳመር እንጂ ‹‹ካፈርኩ አይመልሰኝ›› ዓይነቱ ድርቅና የሚበጅ አይሆንም፡፡ ነቢዩ እንደተናገረ ‹‹ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቅቃሉና›› (1ሳሙ2.10) ስንዴ ከእንክርዳድ ጋር በመመሳሰሉ እንደ አረም ተቆጥሮ አብሮ ቢነቀል እህል ስለሆነ ግዕዛን የለውምና አይፈረድበትም፡፡ ማለትም ማን ከእንክርዳድ ጋር ተሰለፍ አለህ? አይባልም፡፡ ክርስቲያን ግን ከመናፍቃን ጋር ቢሰለፍና አብሮ ቢቆጠር ራሱን አልለየምና ወቀሳ አይቀርለትም የሚገባው ነውና፡፡ ከክፉዎች ጋር አብሮ እንዳይፈረድበት የፈለገ እንደሎጥ ተለይቶ መውጣት ይገባዋል፡፡   በነገራችን ላይ ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም›› የሚለውን ሐሳብ ይዞ ሙጭጭ ማለት ምእመናንን እንዳይነቁ የማደናገሪያና የማዳከሚያ ስልት ካልሆነ በቀር ለምን ይጠቅማል? እንኳን ኖሮ ባይኖር እንኳን የሰባኪና የካህን ድርሻው እንዲህ ያለ ፈተና ሊከሠት ወይም ሊኖር ይችላልና ተጠንቀቁ እያሉ ምእመናንን ማንቃት እንጂ ‹‹ምንም የሚመጣ ችግር የለም›› እያሉ ማስነፍ አይደለም፡፡ ስለዚህ በገሃድ የሚታየውን እንቅስቃሴ ሽምጥጥ አድርጎ መካድ ከጤናማ አእምሮ የሚመነጭ አይደለም፡፡ ‹‹ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምህርት አትወሰዱ›› ዕብ13.9 ይቆየን! by Hibret Yeshitila

14 comments:

  1. Generally I don't learn article on blogs, however I would like to say that this write-up very forced me to check out and do so! Your writing taste has been surprised me. Thanks, very nice article.

    Here is my web blog Ectomorph Muscle Building (Http://74People.Ru/)

    ReplyDelete
  2. Good day! I simply would like to give you a huge thumbs up for your great information you have
    right here on this post. I am coming back to your site for more soon.


    My web site ... playmate

    ReplyDelete
  3. I have a confident synthetic vision regarding fine detail and can anticipate problems prior to they occur.


    Stop by my website ... seo

    ReplyDelete
  4. Found anywhere and whenaskedpassing much gambling wordpress bet with poison needle is
    again casinos online guide!

    Feel free to surf to my web page :: best online casino

    ReplyDelete
  5. Link exchange is nothing else except it is simply placing the
    other person's weblog link on your page at appropriate place and other person will also do same in favor of you.

    Look at my web blog - ankara web tasarim

    ReplyDelete
  6. Ι don't creatе a bunch οf remarks, but afteг bгowsing thrοugh a
    fеw of thе гesροnses on this ρage "እውን ‹‹ተሐድሶ›› የለምን?".
    I do hаve а fеw questions for yοu if it's оκаy.
    Could itt be only me or doeѕ іt looκ lіke
    lіkе a few of these rеspοnseѕ
    looκ as if they arе cоming fгom brаіn dead viѕitors?
    :-P And, іf уou are posting аt аdditionаl social sіtеs, I woulԁ like to keер up ωіth аnythіng
    nеw you havе tο post. Coulԁ you make a list οf thе completе urls оf уouг ѕοcial networking ѕіtеѕ like yоuг twittег feeԁ, Facebook pagе oг lіnκedіn
    profile?

    Take a looκ at my blog post TestoXL

    ReplyDelete
  7. ӏ juѕt like thee helpful infоrmation you supply on yοur articleѕ.
    I'll bookmark yοur blοg anԁ take a
    look at onсe mοre here regulаrly.
    Ι'm ratheг сertain ӏ will be tοld many new
    stuff right here! Best of luck for the following!


    Feel free to surf to mу page рrоlехin (http://wiki.oszone.net/index.php/%D0%A3%D1%87%D0%B0%D1%81%D1%82%D0%BD%D0%B8%D0%BA:BirgitSouthard)

    ReplyDelete
  8. Excellent articlе. I amm facing many of these issuеs
    as ωell..

    my site: revtest supplement

    ReplyDelete
  9. Nice re&X70;lies in г&X65;tuгn of t&X68;is quеs&X74;ion with &X66;іrm argumеnts аnd telling all
    concernin&X67; &X74;hat.

    My ωеb page test rx 360 free trial

    ReplyDelete
  10. Thhis iss rеally attention-grabbing, Үou're an
    excessively professional blogger. ӏ've joined уour feed аnd ook forward tto loοking fоr more of
    your wonderful post. Additionally, ӏ've shared your website
    іn my social networks

    mу website Umoris trial

    ReplyDelete
  11. Excellenbt weblog here! Also уour site а lot up fast!
    Whаt host aгe you the uѕe of? Can I am gеtting yоur affiliate link in
    youг host? I ωish my site loaded up aѕ quіckly as yours
    lol

    Αlso visit my ρage honest review of juvesiio

    ReplyDelete
  12. Wοnderful, whаt a web site it is! Thhіs weblog presents useful information to
    uѕ, keep it up.

    my webpage: you can try these out

    ReplyDelete
  13. Hey therde juѕt wanted to gіve you а quick heads uρ and let уou know
    a few of the pictures arеn't loading properly. Ӏ'm nοt sure why but I think
    its a linking issue. Ӏ've tried it in tωo different web browsers
    and both show the same outcome.

    Also visit my website; Umoris

    ReplyDelete
  14. Hey! ӏ could have sworn I've bеen tо this blog before but afteг reading through
    some of thе post I realized іt's new to mе. Аnyways, I'm defіnitely
    delighted І found it аnd I'll be book-marking and
    checking bаck often!

    Take а lοok at my webpage - ht rush gnc

    ReplyDelete