Tuesday, August 23, 2011

መለየትን የሚወድ ምኞቱን ይከተላል. ምሳሌ ም .18 ቁ. 1


መለየትን የሚወድ ምኞቱን ይከተላል..
ምሳ ም 18 ቁ 1
"የሞት አያት ማነው?" ብለው በአንድ ወቅት መምህራችን ጠየቁን ሁሉም ለመመለስ አጁን አወጣ፡፡ በጣም ተደነኩ አኔ ግን "ደሞ ለሞትም የዘር ሀረግ አለው እንዴ ?"ብዬ መልሱን ለመስማት ቸኮልኩ፡፡ ብዙዎቻችሁ መልሱን እንደምታውቁት እገምታለሁ፡፡ ግን መልሱን ከማወቃችሁ በፊት ለዚህ ጥያቄ ምን አይነት ምላሽ ትገምቱ ይሆን? አኔ መልሱ እስኪመለስ ባለው ጊዜ በጣም ብዙ ነገር አሰብኩ፡፡ አኔ ካሰብኩት አንዱም መልስ አልነበረም፡፡
በሐዋርያው በቅዱስ ያዕቆብ መልእክት ምዕ 1 ቁ 12-15
"በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።  ማንም ሲፈተን። በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል፤ እግዚአብሔር በክፉ አይፈተንምና፤ እርሱ ራሱስ ማንንም አይፈትንም ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል።  ከዚህ በኋላ ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች፤ ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች።"
ንግዲህ የሞት አያቱ ምኞት ነው ማለት፡፡ መጽሐፍት አንደሚነግሩን
ዘፍ ም 3 ቁ 3-6"… እባብም ለሴቲቱ አላት። ሞትን አትሞቱም፤ ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።
ሔዋን ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ አየች(ተመኘች) ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ወለደች ማለትም ሔዋን ቆርጣ በላች (ሕገ እግዚአብሔርን አፈረሰች) የኃጢአት ደሞዙ (ልጅ) ሞት ነውና ሞት ተፈረደብን፡፡ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በሞቱ ሞትን ሽሮልናል፡፡
አሁን በዚህ ዘመን ምኞታቸውን በመከተል መለያየትን በቤተክርስቲያናችን ለመፍጠር የሚጥሩ አንድና ሁለት አይደሉም፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን እንዳለ የራሳቸውን ክብር አንጂ የቤተክርስቲያን ጉዳይ ምናቸውም ያልሆነ በአጠቃላይ ምኞታቸውን ብቻ የሚከተሉ አባቶችን ከራሳቸው አሳንሰው ራሳቸውን ከፍ አድርገው የቤተክርስቲያን ልጆች እኛ ብቻ ነን የሚሉ (------እኔን ወለደች እገሌን ወለደች -------) ናቸው፡፡ "በልቡ ያለውን ሁሉ መግለጥ ብቻ ይወድዳል እንጂ" ምሳ ም 18 ቁ 2
አነዚህ ሰዎች በጣም የሚገርም ነገራቸው "ለካ ትወዱናላችሁ ለካ ታከብሩናላችሁ ለካ እኛ ብንወድቅ ይህ ሁሉ ሕዝብ ይወድቃል" እያሉ ህዝቡን በምላሳቸው በቃ ምን አለፋችሁ ሁሉም ነገር ምላሳቸው ላይ ነው ያለው፡፡ የቤተክርስቲያንን ፍቅር፤ የሕዝብ ፍቅር ----ወዘተ በምላሳቸው ምላስ ብቻ፡፡ ግን በተጨማሪ ምላሳቸው ከዚህ የተለየም ነገር አለው፤ ስድብ ፡፡ አትሳደቡ ብለው ግን አስተምረውን ያውቃሉ፡፡ ደሞ የት እንደሚሳደቡ ታውቃላቸሁ አውደ ምሕረት ላይ ቆመው፡፡ ምሳሌ (የንፍሮ ቀቃይ ልጅ፣ ……………………..) ከዚህም በላይ እኔ በጣም በእውነት እላችኋለሁ በጣም አዝናለሁ በአውደ ምሕረት ላይ "የጥፋት ርኩሰት ቆሞ ስታዩ ያኔ ሰሚው ያስተውል" 
አነዚህ ሰዎች እውነት አውደ ምሕረት ላይ ራሳቸውን ሳያርሙ፤ የሰደቡትን ሕዝብ ይቅርታ ሳይጠይቁ፤ ሳይማሩ(መቼም ምሥጢራተ ቤተክርስቲያንን ሳያውቁ እንደ ሚያውቁ ሆነው ሲያስተምሩ ሰምተናል ብዬ ነው) ማስተማር አለባቸው ትላላችሁ????
                                                የገዛ ምኞታችንን ከመከተል
የአግዚአብሔርን መልካም ፈቃድ እንድናውቅ
              ፈቃዱንም እንድንተገብር አግዚአብሔር ይርዳን!
የቅዱሳን አባቶቻችን ጸጋ በረከታቸው
ጥርጥር የሌለባት ሃይማኖታቸው
ድል የማትነሳ እምነታቸው
ከአኛ ከሁላችን ጋር ትሁን አሜን!!!!!!!!!

1 comment:

  1. enezih ye tekula lijoch manintachewin begilitsi eyasayu new.ewinet yebetekiritian lijoch bihonu noro nisiha gebitew,subae yizew,erasachewin zik adirgew,..egziabherin belemenu neber.neger gin alamachew betekirtianin mebetibet silenebere bota eyakeyayeru yewahun hizib yateramsalu.Gin baywikut enji medhanialem betekiristianin silemitebikat enesu yitefalu

    ReplyDelete