Monday, December 19, 2011

ገዳመ አስቄጥስ

ጉብኝት ወደ ገዳመ አስቄጥስ

አባ መቃርዮስ

በአንድ ወቅት አባ መቃርዮስ ይህንን ታሪክ ተናግሮ ነበር። ወጣት ሆኘ በአንዲት በዓት ውስጥ ስኖር መንደሩ ጸሐፊ ሊያደርጉኝ ፍለጉ። ይህንን ክብር መቀበል ስላልፈለኩ ሸሽቼ ወደ ሌላ መንደር ገባሁ። ሸሽቼ ስሔድም አንድ ሰው አብሮኝ ነበረ። ያም ሰው እኔ በእጄ የምሰራውን እየሸጠልኝ ያገለግለኝ ነበር። በዚህ መሐል በዚያ መንደር የምትኖር አንዲት ድንግል የነበረች ሴት ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ አርግዛ ተገኘች። ማርገዟም በታወቀ ጊዜ ከማን እንደጸነሰች ቤተሰቦቿ አጥብቀው ጠየቋት። እሷም የደፈረኝ እና የጸነስኩትም ከዛ መናኝ ሰው ጋር ብላ ነገረቻቸው። ቢዚህን ጊዜ መንደርተኞችም ሲሰሙ በፍጥነት መጥተው ያዙኝ። በጣም ጥቁር የመሰለ ማሰሮ እና ሌሎችንም የወዳደቁ ነገሮች በአንገቴ ዙሪያ አጠለቁብኝ ከዛም ወደ መንደሮችና አደባባዮች እያዳፉ ወሰዱኝ። በጣምም አብዝተው ይደበድቡኛል። ደግሞም « ይህ መነኩሴ ልጃችንን አበላሸ፤ ያዙት፤ በሉት እያሉ ይቀጠቅጡኛል» ብዙም ክፉ ቃላትን ይናገሩ ነበር።
እስከ ሞት ድረስ ደበደቡኝ። ከሽማግሌዎች አንዱ ወደ እኔ ቀረበና « ምን እያደረጋችሁ ነው ምንስ መስራታችሁ ይህን እንግዳ መነኩሴ መከራውን የምታሳዩት ደግሞስ እስከ ሞት ድረስ እንደዚህ የምትደበድቡት» ምክኒያታችሁስ ምንድን ነው ብሎ ጠየቃቸው። እኔን ያገለግለኝ የነበረ ሰው በሃፍረት ስሜት ውስጥ ሆኖ በኋላየ ይከተለኝ ነበር። እሱም እኔን እንደሚያገለግለኝ ያውቁ የነበሩ ሰዎች እርሱን ይሰድቡት ነበር። « ተመልከት ይህንን አብዝተህ ታምነውና ታገለግለው የነበረው መነኩሴ እንደዚህ አሳፋሪ፤ ዘግናኝ እና አስነዋሪ ስራ በንጹህ ልጃችን ያደረገውን ስራ? አያሳፍርም? ምን እንደሰራ አየህ? ይሉት ነበር። የልጅቱም ወላጆች « ልጃችንን ለመንከባከብ ቃል እስኪገባ ድረስ እንዳትለቁት» ብለው ትዕዛዝ አስተላለፉ። እኔም ያንን ትዕዛዝ ሙሉ በሙሉ እንደምፈጽምላቸው ቃል ከገባሁላቸው በኋላ ወደ ቤተ እንድሄድ ፈቀዱልኝ። እኔም ከዛ መከራ፤ ስቃይና እንግልት እንደተላቀኩ ባየሁ ጊዜ አምላኬን አመስግኜ ወደ በኣቴ ተመለስኩ። ከዚያም የሚያገለግለኝን ሰው « ያለኝን ቅርጫቶች ሽጥና ለዚያች ሴት ስጥልኝ» አልኩት እርሱም እንዳልኩት አደረገ። ለራሴም መቃርዮስ ሆይ ለራስህ ሚስት አግንተሃል፤ እርሷን መንከባከብ ትችል ዘንድ ካለፈው የተሻለ ስራ መስራት አለብህ ብየ ለራሴ ነገርኩት። ከዚያም ሌትና ቀን መስራት ጀመርኩ። ያፈራሁትንም ገንዘብ ለልጅቷ እየላኩ መርዳት ጀመርኩ። ለብዙ ጊዜ እንደዚህ እያደረኩ መውለጃዋ ጊዜ እስኪደርስ ድረስ እረዳት ነበር። የመውለጃዋ ቀን በደረሰ ጊዜ ምጡ በዛባት ለብዙ ቀናት ብታምጥም መውለድ ግን አልቻለችም ነበር። « መንደርተኞችም ተሰባሰቡ፤ ተጨነቁ ደግሞም እርስ በእርሳቸው ይነጋገሩ ጀመር ምንድን ነው ችግሩ እያሉ። የልጅቷ ምጥም እየበዛ፤ እየተሰቃየች በመጣች ጊዜ ምንድን ነው ችግሩ? ብለው እሷን ጠየቋት። እሷም « ምክኒያቱን አውቄዋለሁ፤ ያንን መናኝ ባልፈጸመው ድርጊት ስለ ወነጀልኩት ነው የጸነስኩት ከሱ አልነበረም፤ የጸነስኩት ከእገሌ ነው ብላ እውነቱን ከእንባ ጋር ነገረቻቸው። በዚህን ጊዜ ያገለግለኝ የነበረው ሰው በጣም ከመደሰቱ የተነሳ እይሮጠ ወደ እኔ ፈጥኖ መጣና የምስራች ብሎ ሁሉን ነገር ገልጦ ነገረኝ። ያች ሴት የጸነስኩት ከመነኩሴው አይደለም እስክትልና እውነቱን እስክትናገር ድረስ መውለድ አልቻለችም ስለዚህ እንደዚያ ሲያሰቃዩህ የነበሩት መንደርተኞች በሙሉ መጥተው ይቅርታ ሊጠይቁህ በዝግጅት ላይ ናቸው አለኝ። ነገር ግን ይህንን ስሰማ ሕዝቡ ስለ እኔ መልካም በማውራት ነብሴን በውዳሴ ያዝሏታል ብየ በመፍራት ሸሸሁ ወደ ሌላ ገዳምም ሄድኩ። ስለዚህ እኛ ከዚህ ምን እንማራለን? ሰውን በሃሰት ከመክሰስ፤ ከመውንጀል መታቀብ ይኖርብናል። ለዚህም እግዚአብሔር አምላካችን ይርዳን። የአባታችን የመቃርዮስ በረከታቸው እና ረድኤታቸው አይለየን አሜን።




No comments:

Post a Comment