Wednesday, January 18, 2012

ለጣቱ ቀለበት እሰሩለት ሉቃ.15፤22

ለጣቱ ቀለበት እሰሩለት ሉቃ.15፤22 
በመምህር ተስፋዬ ሞሲሳ
የጠፋው ልጅ  (ሉቃስ 15:11)
አባቴ ሆይ መጥቻለሁ
ይቅር በለኝ በድያለሁ
ይቅር ባይ ነህና የበደሉህን
ቂም እንዳቲዝብኝ በደሌን ቆጥረህ
ስለማይገባኝ ለመባል ልጅህ
ቁጠረኝ እንዳንዱ ከአገልጋዮችህ

አባቴ ሲቆጣኝ አልመለስ ብዬ
ስትመክረኝ እናቴ አልሰማሽም ብዬ
ከወንድሜ ጋራ ሀብቴን ተካፍዬ
ከሰው ሃገር ሄድኩኝ ከአባቴ ተለይቼ

የማይጎዳ መስሎኝ የሃጥያት መከራ
ኮብልዬ ነበረ ወደ ሃጥያት ተራ
አሁንግን ተመለስኩ ጥፋቴን አውቄ
የሰማይ አባት ሆይ ይቅር በለኝ

በአባቴ ቤት ሞልቶ ማርና ወለላ
በአባቴ ቤት ሞልቶ የቅኔው አዝመራ
ሄድኩኝና መንገድ በሰፊው ጎዳና
ናፍቆቱ በዛብኝ ያሬዳዊው ዜማ

እኔም ልብ ስገዛ ስመለስ ከቤቴ
ገና ከሩቅ አይቶኝ ይቅር ባይ አባቴ
ወደኔ ሮጦ አቀፈና ሳመኝ
በልቤ እየገረመኝ ወዲያው መታቀፌ
ትንሽ ሊወቅሰኝ ነው ብዬ ስጠባበቅ
መች እሱ ሊያስታውስ የትላንቱን ዛሬ
ደገመና አዘዘ አዲስ ልብስ ለእራሴ
ደግሞም ቀለበት ለጣቴ ; ጫማንም ለእግሬ

ይቅር ባይ ነህና የበደሉህን
ቂም እንዳቲዝብኝ በደሌን ቆጥረህ
ስለማይገባኝ ለመባል ልጅህ
ቁጠረኝ እንደ አንዱ ከአገልጋዮ

1 comment:

  1. Incredible points. Great arguments. Keep up the amazing spirit.


    Here is my page windows gadget calendar ()

    ReplyDelete