Thursday, May 17, 2012

ማ/ቅዱሳን መንግሥት በዋልድባ አካባቢ ስለሚገነባው የስኳር ፕሮጄክት “መልካምነት” ባለመዘገቡ ተጠየቀ፤ መልስ እንዲሰጥ ይጠበቃል


አስከትሎም “ስለሆነም ማንኛውም ጋዜጠኛ በተለይም ደግሞ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልሣን የሆነው የማኅበሩ ጋዜጣና መጽሔት መረጃ ከወሰደ በኋላ መግለጫውን አለማውጣቱ አግባብነት የሌለው ከመሆኑም በላይ የሚዲያ ሥነ ምግባርንም ያልተከተለ ስለሆነ” ጽሑፉ ያልወጣበትን ምክንያት ማኅበሩ በጽሑፍ ይገልጽ ዘንድ ከሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መታዘዙን ያብራራል።

የመምሪያው ደብዳቤ አክሎም “ጋዜጣዊ መግለጫውን በሚዲያ ለማውጣት ተስማምታችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ ከወሰናችሁ በኋላ ዘገባው የቀረበት ምክንያት በጽሑፍ ለማደራጃ መምሪያው” እንዲመለስ እንደሚጠብቅ ይገልጻል። ደብዳቤው በአድራሻ ለማኅበሩ ከተላከ በኋላ ደግሞ ለቤተ ክህነቱ የተለያዩ አካላትና በመንግሥትም በኩል “ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር፣ ለብሔራዊ ደኅንነት አገልግሎትና ለፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን” ግልባጭ ተደርጓል።

የቅ/ሲኖዶስ ጽ/ቤት፣ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት. የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት፣ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ እና ሕግ አገልግሎት መምሪያ የቤተ ክርስቲያናችን አካላት ስለሆነ በቀጥታም ባይሆን ጉዳዩ ሊያገባቸው ይችላል። ከላይ ስማቸው የተዘረዘሩት የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በምን አግባብ ነው ስለ አንድ ማኅበር፣ ያውም በአንድ መምሪያ ሥር ስላለ አካል ግልባጭ የሚደረግላቸው? መንግስታዊ መሥሪያ ቤቶቹ ከሚዲያ ጋር የተገናኙ እንኳን ቢሆኑ በግድምድሞሽ “ግንኙነት አላቸው” ይባል ይሆናል። ፌዴራል ጉዳዮች፣ ደኅንነት፣ ፖሊስ … መጠቀሳቸው ለምን ያስፈልጋል? እሰሩልን፣ ግደሉልን፣ ቀፍዱድልን ለማለት ካልሆነ።


በእውነት በአገሩ ሕግ የለም ማለት ነው? በየትኛው አገር ነው አንድ ጋዜጠኛም ሆነ የሚዲያ ተቋም ስለዘገበው ሳይሆን ስላልዘገበው ነገር የሚጠየቀው? ስለጻፈው ሳይሆን ሳይጽፍ ስለቀረው የሚፈረድበት? ይህ በዓይነቱ በየትም ዓለም ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቀው ክስ መጨረሻው ምን እንደሚሆን ለማወቅ በጣም ያጓጓል። ደብዳቤው “የጋዜጠኝነት ሥነ ምግባርን ማጉደል” ያለውን ይህንን ላልጻፉት ጽሑፍ የመወንጀልን ጉዳይ በዓለም የጋዜጠኝነት ታሪክ ውስጥ በብቸኝነቱ ሊያስመዘግብ የሚችለውን ጉዳይና ውጤቱን ወደፊት የምናየው ይሆናል።

ብራቮ ቤተ ክህነት!!!!!

ቸር ወሬ ያሰማን፣
አሜን (ምንጭደጀ ሰላም፤ ግንቦት 9/2004 ዓ.ም፤ May 17/ 2012)




3 comments:

  1. THE ANSWER SHOULD BE AS FOLLOWS: THE PROJECT HAS SHORT AND LONG TERM DESTRUCTIVE EFFECT ON THE MONASTERY. SO, MK OPPOSES ANY PROJECT TO BE CARRIED OUT IN AND AROUND THE MONASTERY BY THE GOVERNMENT OR OTHER INVESTORS. MK FIRMLY BELIEVES THAT IT SHOULD BE ONLY THE CHURCH THAT HAS THE RIGHT TO UNDERTAKE ANY DEVELOPMENTAL PROJECTS IN THE VICINITY OF THIS HOLY PLACE.

    ReplyDelete
  2. Nice blog! Is your theme custom made or did
    you download it from somewhere? A design like yours with a few simple tweeks would really make my blog shine.
    Please let me know where you got your design. Thanks
    my web page - cool articles to write about

    ReplyDelete
  3. The second is usually to create a sitemap to all your internal pages and hyperlink
    to it out of your homepage. edu best at determining true link quality and
    bad links can hurt crawl depth. If your online designer struggles to show high rankings for the site, it's once again time to change hands.
    My site : http://proimblogger.com/bookmarking-demon-review/

    ReplyDelete