ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አባዊነ!
ከመስከረም26- ኅዳር 6 - ዘመነ-ጽጌ
†♥†
“ተዘከር እግዚኦ ከመመሬት ንሕነ ወሰብዕሰ ከመሣዕር መዋዕሊሁ ወከመ
ጽጌ ገዳም ከማሁ ይፈሪ” †♥† (((መዝ.፻፪/፻፫፡፲፬-፲፭
(102/102፡14-15)))
ትርጉም፡- “አቤቱ፥
እኛ
አፈር
እንደ
ሆንን
አስብ።
ሰውስ
ዘመኑ
እንደ
ሣር
ነው፤
እንደ
ዱር
አበባ
እንዲሁ
ያብባል፤”
(((መዝ.፻፪/፻፫፡፲፬-፲፭ (102/102፡14-15)))
†♥† ሁሉን ቻይ ታላቅ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፣ በቀንና
በሌሊት የአንተን መኖር አስታውስና፣ አንተን ሁል ጊዜ በፊቴ አደርግህ ዘንድ ልቤን ምራልኝ፤ በኪሩቤል ላይ የምትኖር የቀለያትንም
(ጥልቅ ባሕርንም) ጥልቀት የምትመለከት ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ፤ አቤቱ ምስጢርን ግለጽልኝ፤ ቃልህንም እናገር ዘንድ፣ ያለመሰልቸት ስለ
አንተ እንድመሰክር አንተ አንደበት ሁነኝ አሜን።”

†♥†
“ጽጌ”
ማለት “አበባ” ማለት ሲሆን “ዘመነ ጽጌ” ማለት “የአበባ ዘመን” ማለት ነው፡፡ በሀገራችን መስከረም 25 ቀን ዘመነ ክረምት አልፎ መስከረም 26 ቀን ዘመነ ጽጌ ይጀምራል፡፡ ዘመኑ አበቦች የሚያብቡበትና ሜዳዎችንና ተራሮችን የሚያስጌጡበት ዘመን ነው፡፡ ፍሬ የተባለ ጌታን ያስገኘች እመቤታችን በአበባ ትመሰላለችና ዘመኑ የጌታንና የእመቤታችንን ነገር በአበባና በፍሬ ለመመሰል የተመቸ ነው፡፡ ስለዚህም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከመስከረም 26 ቀን ጀምሮ እስከ ኅዳር 6 ቀን ድረስ የጌታን እና የእመቤታችን ስደት ታስባለች፡፡ በዚህ ዘመን ቅዱስ ያሬድ እና አባ ጽጌ ድንግል ባዘጋጇቸው ድርሰቶች የጌታችን እና የእመቤታችን ስደት በማኅሌት ይታሰባል፤ ምስጋና እና ልመና ይቀርባል። ምእመናን ቤተ ክርስቲያናቸው በሠራችላቸው ሥርዓት መሠረት በፍቅርና በደስታ ይዘክሩታል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስደቱን ለማሰብና በረከት ለማግኘት በርካታ ክርስቲያኖች የአዋጅ ጾም ባይሆንም በፈቃደኝነት ዘመኑን በጾም ያሳልፉታል፡፡