Thursday, November 17, 2011

በአቡነ ፋኑኤል ሥርዓት አልበኝነት የተቃውሞ ሕዝባዊ ጥሪ ለመላው ዓለም



ለዋሺንግተን ዲሲ እና አካባቢው ነዋሪዎች በሙሉ!

አቡነ ፋኑኤል በገጠማቸው ቀውስ እንዳዘኑ!
 ከትላንት በስቲያ ሰኞ ከቀትር በፊት አቡነ ፋኑኤል በድብቅ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ገብተው ማደራቸው ተዘግቧል፥ በእለት በገቡበት ዕለት ከፍተኛ ተቃውሞ እንደሚገጥማቸው ተገምቶ ስለነበር ቀድመው ለሰዎች ሐሙስ ብለው በሀሰት ፕሮፓጋንዳ አስነግረው ነገር ግን እሳቸው ሰኞ ከእኩለ ቀን በፊት ማንም ሳይሰማ ወደ ከተማው ገብተው አድረዋል። በዚሁ እለት በቨርጂኒያው አየር ማረፊያ እንደደረሱ አጠገባቸው ሆነው እርሳቸውን እና አላማቸውን በመደገፍ የሚታወቁት የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካሕናት እንዲሁም ከአካባቢው ካሕናት እነ ቀሲስ ታደሰ ሲሳይ እና በቀሲስ ኢስሃቅ አማካኝነት ከአየር ማረፊያ ተቀብለዋቸው በቀጥታ በደቡብ ምዕራብ ዋሽንግተን  ወደሚገኘው የደብረ ምሕረት ገንዘብ ያዥ ወደ ሆነው ሰው መኖሪያው ቤት በቀጥታ አምርተው በዛው ቀናትን ለማሳለፍ ተገድደዋል። ባለፈው እንደዘገብነው በዚህ ጉዞዋቸው በጋሻውን ይዘው ለመምጣት ብዙ ጥረቶችን ለማድረግ ቢሞክሩም የተሳካላቸው አይመስልም፣ ነገር ግን እርሱን ለማምጣት የሚቻላቸውን እንደሚያደርጉም ቅዱስ ፓትሪያሪኩም ቃል እንደገቡላቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ።
አንድ የአካባቢው ክርስቲያን በዛሬው ዕለት በላከልን መልዕክት እንደሚያስረዳን በመጪው እሁድ የሚከበረውን የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ለማክበር የመጡት አቡነ ፋኑኤል ከባድ ተቃውሞ እንደሚገጥማቸው ከወዲሁ በመረዳት የደብሩ የቦርዱ አባላት አስቸኳይ ስብሰባ አድርገው የሚከተሉትን መመሪያዎች አስተላልፈዋል

፩ኛ/ በክብረ በዓሉ ቀን ማንም ሰው መኪናውን በጊቢው ውስጥ እንዳያቆም (ለጸጥታ ስለማይመች)
፪ኛ/ ከአካባቢው የፓሊስ ቢሮ ከሁለት እስከ አራት የፓሊስ ሰራዊት በቦታው ተገኝቶ ክብረ በዓሉን እንዳይታወክ እንዲቆጣጠሩ
፫ኛ/ አቡኑም ምንም አይነት ንግግር እንዳያደርጉ
፬ኛ/ ቢቻል በዑደቱም ላይ ባይኖሩ የሚሉትን መመሪያዎች አስተላልፏል።

ከዚህ የቦርዱ መመሪያ እንደምንረዳው በደብረ ምሕረት አካባቢ አቡኑ ከመጡ ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ አለመረጋጋት እና መሸበር እንዳለ ከአካባቢው መረጃውን ያደረሱን ክፍሎች ያስረዳሉ። በተያያዘ ዜና በዚሁ እሑድ በሚደረገው የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ላይ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ተቃውሞ እንደሚደረግ ከዚህ ጋር አያይዘው ገልጸውልናል፣ በመጪው እሑድ ከፍተኛ ትዕይንቱን በማዘጋጀት ላይ ያሉት ወገኖቻችን እንዳስረዱን ከሆነ አላማቸውን በግልጽ አስቀምጠው የአቡነ ፋኑኤልን አስተዳደርም ሆነ ውክልና አንቀበልም። ልክ እንደ ከዚህ በፊቱ በተለያዩ የሀገራችን የኢትዮጵያ ክፍሎች ተመድበው ሥራ ከመስራት ይልቅ መከፋፈልንን እና ሕዝብን በሕዝብ ላይ በማነሳሳት ሥራ ላይ ተሰማርተው አብሮ ለብዙ ዘመን የኖረውን ሕብረተሰብ ለያይተው ሲያበቁ እርሳቸውም ከሀገረ ስብከታቸው በሕዝቡ ብሶት እና በቅዱስ ገብረኤል ረዳትነት ከቦታቸው ተነስተዋል። እዛ በነበሩባቸው ጊዚያት አቡነ ፋኑኤል "እኔ አሜሪካው ነኝ ምንም ልታደርጉኝ አትችሉም" እያሉ በደሃው ሕዝብ ላይ ሲንቀባረሩ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፣ ሆኖም በአሁን ሰዓት ቤተ ክርስቲያንንም ወክለው ይሁን በገንዘብ ገዝተውት ወደ ዋሺንግተን አመጣታቸውንም ሆነ ውክልናቸውን እንደማይቀሉ አስታውቀው፣ ጥያቄያቸውንም በአቸኳይ የማይመልሱ ከሆነ ማንኛውንም እርምጃ ለማድረስ ማንኛውንም ዝግጅት አድርገው ለዚህም ደግሞ በማንኛውም መልኩ የገንዘብም ሆነ የሰው ሃይል በሚገባ ስላላቸው በሕግም ይሁን ከሕግ ውጪ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጅታቸውን እና ቁርጠኝነታቸውን አሳውቀውናል።

በቤተ ክርስቲያኑ አካባቢም ምዕመናኑ፣ አገልጋዮች ካሕናት እንዲሁም ዲያቆናት ለሁለት እነደተከፈሉ ይነገራል። በአገልጋይ ሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በኩል ባለፈው እሑድ ተሰባስበው ግማሹ የሰንበት ት/ቤት ከአየር ማረፊያ ሄደን መቀበል እና ማጀብ ይኖርብናል ሲሉ እንዲሁ ግማሹ ደግሞ አይደለም አየር ማረፊያ ሄደን ልንቀበላቸው እዚህ መቀመጥ የለባቸውም፣ እስከ ዛሬ ድረስ በእንግድነት ነው ተቀብለናቸው ያስተናገድናቸው ከዚህ በኃላ ግን ሥልጣኑን በምንም መንገድ ያግኙት እኛ ከዚህ በኃላ ሊወክሉንም እንደ አባት ልንቀበላቸውም አንችልም በማለት አማረው ተናግረዋል። በአገልካይ ካሕናትም በኩል ገሚሶቹ ምን ችግር አለው ተቀብለን ማገልገል ነው እንደውም እስከ ዛሬ ድረስም የሳቸውን ሥም ነው ጠርተን ሥርዓተ ቅዳሴውንም የምንፈጽመው አሁን ደግሞ ሕጋዊ ወኪል ስለሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ስለላካቸው መቀበል የግዴታችን ነው በማለት በብልጥነት ለማስቀመጥ ይሞክራሉ። ከፊሎቹ ደግሞ የሰንበት ት/ቤቱ ዓይነት ተመሳሳይ አቋም ይዘው እስካሁን ስማቸውን የምንጠራው ከሰሩት ሥራ አንፃር ነው እንዲሁም ባለቤትነቱ የርሳቸው ስለሆነ ነው ይሁንና ከዚህ በኃላ እርሳቸውን እንደ ዋሽንግተን ዲሲ እና የምዕራብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብንቀበል ፓትሪያሪኩን የመቀበል እና በሥርዓተ ጸሎቱ ላይ የመጥራት ግዴታ ሊመጣብን ይችላል፥ ያማለት ደግሞ ሕዝባችንን በጣም ስለሚያስቆጣው ይሄኛው አካሄድ ሊያዋጣን አይችልም በሚል ከፍተኛ ተቋውሟቸውን ግልጸዋል። እንደ መረጃ አቀባያችን አገላለጽ ከሆነ በማንኛውም መልኩ የደብረ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ከዚህ በኃላ ለሁለት ወይም ለሦስት ቦታ የሚከፋፍለው መንገድ እንዳለ በግልጽ አሳይቷል በመሆኑም የአቡነ ፋኑኤል አመጣጣ በማንኛውም መመዘኛ የአካባቢውን ሕዝብ ቀርቶ የደብረ ምሕረትን ሕዝበ ክርስቲያን እንኳ ሊወክሉ እንደማይችሉ ከወዲሁ ተፈርቷል፣ አንዳንድ የቤተ ክርስቲያኗ ሕልውና ያሰጋቸው ምዕመናንም የፊርማ ማሰባሰቢያ እና ደብዳቤ አዘጋጅተው ለወከላቸው ለቅዱስ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲነሱልን ሲሉ ደብዳቤዎችን እና የፊርማ ማሰባሰቡን ሥራ ከወዲሁ እንደጀመሩት ከወዲሁ ለማወቅ ተችሏል።

ከዚህ በተጨማሪ በዚሁ በመጨው እሑድ ህዳር ፲ ቀን (Nov. 20, 2011) ማለትም የቅዱስ ሚካኤል በዓለ ንግስ እለት ታላቅ የሆነ ሕዝባዊ ተቃውሞ እንደሚያደርጉ እና አስፈላጊውን ሁሉ ቅድመ ዝግጅት አድርገው እንደጨረሱ እና የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ እርዳታ እና ትብብር በመጠየቅ አስፈላጊውን ትብብር እንዲደረግላቸው ከወዲሁ ጥሪ እንድናደርግላቸው ከመልዕክቱ ጋር ተያይዞ ደርሶናል። በዚህ ሕዝባዊ ተቃውሞ ላይ እያንዳንዱ ሀገር ወዳድ እና የኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያኑ ሥርዓት ግድ የሚለው ሁሉ የዚህ ሕዝባዊ ተቃውሞ ተካፋይ እንዲሆን ከወደሁ አዘጋጆቹ አስቀድመው ጥሪያቸውን አድርሰውልናል። የዚህ ዝግጅት አስተባባሪዎች እንደገለጹልን ከሆነ አቡነ ፋኑኤል እና ተባባሪዎቻቸው ይሄንን ክብረ በዓል ተጠቅመው የቪዲዮ ቀራጭ ባለሙያ ግምቱ $2000.00 ብር ከፍለው በቪዲዮ አስቀርጸው እና አቀናብረው ልክ ሕዝቡ እንደተቀበላቸው አስመስለው "ሕዝቡ ተቀብሎናል ሃሳብ አይግባችሁ" ብለው ፕሮፓጋንዳቸውን ለመሥራት እና ወደ ኢትዮጵያም ለመላክ ቅድመ ዝግጅትም እያደረጉ እንደሆነ ከወዲሁ ለመረዳት ተችሏል። አባ ፋኑኤል እና ግብረ አበሮቻቸው እንዲህ ዓይነት ትውልድን የማያንጽ ሥራ እየሰሩ፣ ጽድቅ ያይደለ ተንኮል፣ እውነት ያይደለ ሐሰት የተሞላበት እየሰሩ እንደገና ልክ በጣም ትጉህ የሆኑ ዓይነት መለስ ቀለስ በማለት ሰውን ለማወዳበድ የሚያደርጉትን ሤራ እና ተንኮል ከወዲሁ ልንገነዘብ ያስፈልጋል እንላለን። አሁንም ሥራ ሰርተናል ብለው ለማለት እንዲህ አይነት ድራማ በማን ላይ የሠሩ እንደሆነ ያልተገነዘቡት እነዚህ ክፍሎች ከተንኮል ይልቅ፣ ትህትና፣ ከበደል ይልቅ ፍቅርን ቢማሩ እና ቢያስተምሩ ይሻላል እንላለን። እነዚህን ሁሉ የተንኮል እና የድራማ ዝግጅቶችን ለመሥራት መዘጋጀታቸው በራሱ እራሳቸውን እና ሕሊናቸውን እያታለሉ ጊዜያቸውን ለመፍጀት ያሰቡ አባት እንጂ ለሥራ የመጡ አባት እንዳልሆኑ ይሄ ሥራቸው እራሱ ትልቅ ምስክር ነው በማለት አዘጋጆቹ በምሬት ገልጸውልናል።

ቸር ወሬ ያሰማን፣ አጽራረ ቤተ ክርስቲያንን ያስታግስልን አሜን
የመላው ዓለም የተዋሕዶ ቤተሰብ

2 comments:

  1. Please change the clour contrast of the page
    pink on black or blue on black is not readable

    ReplyDelete
  2. egzeo egzeo ere ebakachu indew letelat deyablos ege ansete menale hulunem legzabehere bentew ena hulachenem yekrestena ye ye gelachenen beneweta ehay ahuneke twahedo lege kekeresteyan aytebekem mechem teknologew bemechenem indehe aynete kefu sera ansreabete indew komeblen inasebe ega manene le ahzabe yebetkresteyan berekeftene nugebuna yetekdesechewen betkresteyan esu waga keflo yakomatene letelate yemneset indew kefu werayse benakom esu lehulum frdun yesete yel

    ReplyDelete