Tuesday, July 24, 2012

መላእክትን ‹‹ያድናሉ›› ማለት ስሕተት ነውን?


ለመሆኑ መላእክት ማዳን ይችላሉ ማለት ስሕተት ነውን? ዛሬ ዛሬ ብዙዎች መናፍቃን መላእክትን ‹‹ያድናሉ›› ማለት እንደ ስሕተትና እንደ ክህደት ቆጥረውት ሲናገሩ መስማት የተለመደ ሆኗል፡፡ ለምን ሲባሉም መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹መዳን በሌላ በማንም የለም›› በማለት ያለ አገባቡ ጥቅስ ይጠቅሳሉ፡፡

በእርግጥ መጽሐፍ ቅዱስ ‹‹መዳን በሌላ በማንም የለም›› ይላል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ መላእክት አያድኑም ማለት አይደለም፡፡  
ቅዱስ ዳዊት በግልጥ ‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፤ ያድናቸውማል›› ይላል፡፡ (መዝ33.7) ጥቅሱ ‹‹ያድናቸውማል›› ማለቱን ልብ በሉ፡፡ መላእክት የማያድኑ ቢሆኑ ኖሮ ቅዱስ ዳዊት በዚህ መልኩ ግልጥ አድርጎ ‹‹ያድናቸውማል›› ይል ነበር? መጽሐፍ ቅዱስ ከመሰከረው እውነት የሚበልጥ ዕውቀት አለንን? እርሱ ‹‹ያድናሉ›› እያለ እኛ ‹‹አያድኑም›› ብንል ምን ማለታችን ነው? ይህ ጥቅስ ውሸት ነውን? ይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል እንታዘዘዋለን? እናምነዋለን? ወይስ ልናርመው እንወዳለን?

በሌላም የመጽሐፍ ቅዱስ ገጸ ንባብ ውስጥ ‹‹ከክፉ ነገር ሁሉ ያዳነኝ መልአክ እርሱ እነዚህን ልጆች ይባርክ›› በማለት ያዕቆብ የልጅ ልጆቹን እንደባረከ እናነባለን፡፡ (ዘፍ48.16) በዚህ ጥቅስ ውስጥ መልአክ ‹‹ከክፉ ነገር ሁሉ›› እንደሚያድን በግልጽ ተጽፏል፡፡ መላእክት ‹‹ያድናሉ›› ላለማለት እነዚህን ግልጽ ቃላት መላእክት ይጠብቃሉ፤ ይራዳሉ፤ ያግዛሉ በማለት ማድበስበስ ይኖርብን ይሆን? ይህ ሁሉ ዝርዝሩ ሥራቸው ቢሆንም እንደሚድኑም ተጽፏልና ማመን ያስፈልጋል፡፡

በዚህ መልኩ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ የተናገረውን ቃል እናቶችና አባቶች በስእለታቸው ‹‹ቅዱስ ሚካኤል አድነኝ፤ ቅዱስ ግብርኤል ድረስልኝ›› እያሉ በመድገማቸው የዋሃን ስለሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ስለማያውቁ ነው መባል አለባቸው? ቅዱስ ዳዊትና ቅዱስ ያዕቆብ የመላእክትን አዳኝነት በግልጽ ያወጁት መጽሐፍ ቅዱስን ወደ መንፈሳዊ ኮሌጅ ገብተው ስላልተማሩ ይሆን? ወይስ አንድ ሰባኪ የመላእክትን አዳኝነት ስላስተማረ ‹‹ገድል ጠቃሽ›› በሚል መጥላላት አለበት? ዘማርያኑስ በዚህ መልኩ መዘመራቸው ሊያስወቅሳቸው ይገባ ነበር?

Friday, July 20, 2012

የ20 ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ ሰማዕት


ሰማዕቱ  አቡነ  ጴጥሮ
« እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡. . . እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» ሰማዕተ ጽድቅ በሆነ ደማቸው አተሙ፡፡  አኩሪ በሆነ አባታዊ ሓላፊነታቸው ለአገር፣ ለቤተክርስቲያን፣ ለወገን ሁሉ አለኝታነታቸው አረጋግጠው ሐምሌ 22 ቀን 1928 .በሰማዕትነት አለፉ፡፡


1875 .. የተወለዱት ኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ የራሷን ጳጳስ  1921 .. በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ ጊዜ ስትሾም አንዱ አቡነ ጴጥሮስ ነበሩ፡፡ የመጀመርያ ጳጳሳት መካከል አንዱ የነበሩት አቡነ ጴጥሮስ፣ "ጳጳስ ዘምሥራቀ ኢትዮጵያ" ተብለው  21 አካባቢዎችን ያስተዳድሩ ነበር፡፡ 

የኢጣሊያ
ፋሺስት 1928 .. በኢትዮጵያ ላይ የግፍ ጦርነትን ባነሣ ጊዜ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ከጦር ስፍራ ለመለየት ስላልሆነላቸው፣ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ተከትለው ወደ ሰሜን ጦር ግንባር ዘምተዋል፡፡ ፋሺስቱ በማይጨው የመርዝ ጦርነት ከማድረጉ የተነሣ፣ የኢትዮጵያ ሠራዊት ሲበታተንም ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር የተመለሱት አቡነ ጴጥሮስ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደው ለአገርና ለነፃነት መሞት ቅዱስ ተግባር መሆኑን ለሥላሴ አርበኞች በመስበክም ይታወቃሉ፡፡
አርበኞች አዲስ አበባን በሁለት አቅጣጫዎች ከሰሜናዊ ምዕራብ  እና በደቡባዊ ምሥራቅ  አቅጣጫ ለመቆጣጠር ውጊያ በከፈቱበት ጊዜ የተማረኩት አቡነ ጴጥሮስ፣ ለፋሺሽት እንዲገዙ የኢጣሊያ መንግሥት ገዢነትንም አምነው አሜን ብለው እንዲቀበሉ ግፊት ቢያደርጉባቸውም፤ እምቢኝ ለሀገሬና ለሃይማኖቴ ብለው ለሰማዕትነት ያበቃቸውን የሞት ጽዋ ተቀብለዋል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ የሆነው ጢሞቴዎስን የተሰጠውን አደራ በመጠበቅ ሓላፊነቱንና ግዴታውን መወጣት እንደ ሚገባው ሲገልጽ «እቀብ ማህጸንተከ፤ አደራህን ጠብቅ» በማለት ነው፡፡ 1ኛጢሞ.6 .2፡፡ ጢሞቴዎስ በመምህሩ የተጣለበትን አደራ ለመወጣት የዚህ ዓለም ፈቃድ ሳያሸንፈው ተወጥቷል፡፡ የዓላውያን ነገሥታት ማዋከብ፣ ድብደባ አደራውን እንዳይወጣ አላደረገውም፡፡ የአቡነ ጴጥሮስ የሰማዕትነትም ጉዞ መነሻውም መድረሻውም የእነዚህ አባቶች አርአያ ፍኖት ነው፡፡

ለሀገራቸውና
ለወገናቸው እስከ መጨረሻዋ ሰዓት ድረስ እውነቱን ከሐሰት በመለየት ለሕዝባቸው የሰጡት ምስክርነት የተጣለባቸውን አደራ ከመወጣት ነው፡፡ አለቃ ተጠምቀ የተባሉ ቅድስናን ከሊቅነት ጋራ አስተባብረው የያዙ የቅኔ መምህራቸው አንድ ቀን ብፁዕነታቸውን ጠርተው የሚከተለውን የአደራ ቃል ያስተላልፋሉ፡፡ «ኀይለማርያም አንተ ወደፊት ጳጳስ ትሆናለህ፤ በወቅቱም አረመኔ በዚህች ሀገር ይሠለጥናል፡፡ ታዲያ ያኔ አንተ ለነፍስህ ሳትሳቀቅ በሰማዕትነት እለፍ፤ ሰማዕትነት ክፍልህ ነው፡፡ አደራ፡፡» /መርሻ አለኸኝ /ዲያቆን/ 1986 .ም፣ ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን፣ ገጽ.80/

ሐዋርያው
ቅዱስ ጢሞቴዎስ የመምህሩን የአደራ ቃል በመያዝ እስከ መጨረሻው እንደጸናው ብፁዕነታቸውም የመምህራቸውን የአደራ ቃል በሰማዕትነት አትመው ጠበቁ፡፡ አንዲትም ቀንና ሰዓት ከሞት ሳይሸሹ እና ሳይደበቁ ለአገራቸው ፣ለቤተ ክርስቲያናቸው እና ለሕዝባቸው ሲሉ ሞትን ተጋፈጡ፡፡ የሰማዕትነትን ጽዋ ተጎነጩ፡፡ የዚህ ምንጩ አደራ ነው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራ የሰጠቻቸውን ሓላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ፣ በትምህርታቸው እያበረቱ አስተዳድረዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሕዝብ ቀስቅሰዋል፤ ራስዎም አምጸዋል፣ ሌሎችንም እንዲያምጹ አድርገዋል በሚል የወንጀል ክስ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ችሎቱ ተሰይሞ ሲቀርቡ ዳኛው «ካህናቱም ሆኑ የቤተክህነት ባለሥልጣናት ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም የጣሊያንን መንግሥት ገዥነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ እርስዎ ለምን ዐመፁ) ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑሲል ጠየቃቸው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በቆራጥነት «አቡነ ቄርሎስ ግብጻዊ ናቸው፤ ስለ ኢትዮጵያና ስለ ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡. . . እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» በማለት ሕያው በሆነ ቃላቸው መለሱ፡፡ ሰማዕተ ጽድቅ በሆነ ደማቸው አተሙ፡፡  አኩሪ በሆነ አባታዊ ሓላፊነታቸው ለአገር፣ ለቤተክርስቲያን፣ ለወገን ሁሉ አለኝታነታቸው አረጋግጠው በሰማዕትነት አለፉ፡፡ / መርሻ አለኸኝ/ዲያቆን/ 1996.ም፣ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን፣ገጽ.77/

Tuesday, July 3, 2012

የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠበቁ ማቴ. 7:15



 
አሸናፊ መኰንን (ዲ/ን)  - አንቀጸ ብርሃን  በሚል ስያሜ በሚያሳትመው መጽሔት ለአብነት ያህል ‹‹በእኛ ቤተ ክርስቲያን አምላክነቱን አጉልቶ የሰውነቱን ቅርበት መዘንጋት፣ በሌሎች አብያተ ክርስቲያናት የሥጋውን ቅርበት አግንኖ የመለኮቱን ክብር መርሳት የተለመደ ነው፡፡ መጽሐፉ ግን ያቻችለዋል፤›› "አባቶቻችን የመፍታትም ሆነ የማሰር ስልጣን የላቸውም " የሚሉና የመሰሉ በርካታ ክሕደቶችን ጽፏል አስተምሮአል፡፡ በመመሪያ ሓላፊ ደረጃ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና መዝገብ ቤት ሓላፊ ከኾነችውና ሙሉ ወንጌልቤተ እምነት ከምታዘወትረው / ዐጸደ ግርማይ ጋራ ጥብቅ ግንኙነት እንዳለው ይነገራል፡፡ በወ/ እጅጋየሁ በየነ አማካይነት በፓትርያሪኩ ልዩ /ቤት መሽጎ በበዓለ ሢመት፣ በዐበይት በዓላት፣ በደቀ መዛሙርት ምረቃ መርሐ ግብሮች ላይ በፓትርያሪኩ ስም የሚተላለፉ መልእክቶችን እስከ መጻፍ መድረሱ ይነገርለታል፡፡ በአሁን ሰዓትም ከበፊቱ በባሰ መልኩ የኑፋቄ ትምህርቱን በመዝራት ተያይዞታል ብዙ ምእመናንንም በማታለል በመውሰድ ላይ ይገኛል። አብረውትም ያሉ ብዙ መናፍቃንና እውነተኛ አባቶች ነን የሚሉ አብረውት ያሉ ሲሆን ምእመናንን ከሚያሳምኑበት አንዱም የቤተ ክርስቲያን አባቶችን በመጥቀስ አብረውት የሚሰሩትን በመጠቆም እነርሱን ጠይቁ እንደሚልም ደርሰንበታል ስራውን ከኋላው ሆነው የሚረዱት በቤተ ክህነት ያለ አንዳንድ አባቶች እንዳሉ ተረድተናል።
 ይህ ሰው ከዚህ በፊትም ብዙ  ምእመናንን ስልጠና እየሰጠ እንደነበርና አሁን ለያዘው የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ስራ ሰፊ እንቅስቃሴ በማድረግ ብዙ ተሐድሶዎችን እንደመለመለ እየመለመለ እንደሆነ  ተረድተናል።
በበለጠ ሙሉ መረጃውን ከበቂ መረጃ ጋር ለወደፊት አናስነብባችኋለን ።
ቤተሰቦቻችሁንና ወንድም እህቶቻችሁን ከእንደዚህ ካሉት መናፍቃን እንዲጠበቁ መከሩ።
መረጃውን በማስተላለፍ የበኩሎን ይወጡ!!!

እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያናችንን ከመናፍቃን ይጠብቅልን።

Monday, July 2, 2012

ለምን አልሰለምሁም? ክፍል ሦስት የቅዱሳት መጻሕፍት ታማኝነት፤


ያለፉት ሁለት ክፍሎች ምስጢር ሥላሴና ምስጢረ ሥጋዌ የተረጋገጡት በቅዱሳት መጻሕፍት ነው፡፡ የቅዱሳት መጻሕፍትን ታማኝነት ለማስተባበል እነዲዳት ሞክረዋል፤ ቁርአን ግን ያረጋግጣል፡፡ሁሉንም እናስከትላለን፡፡ (2ጢም.3 ፡16-17) ቅዱስ መጽሐፍ በሙሉ በእግዚአብሔር መንፈስ መሪነት የተጻፈ ነው፤ እርሱ እውነትን ለማስተማር፤ የተሳሳቱትን ለመገሠጽ፤ ስሕተትን ለማረምና ለትክክለኛ ኑሮ የሚበጀው መምሪያ ለመስጠት ይጠቅማል፡፡ የሚጠቅመውም የእግዚአብሔር ሰው ፍጽም እንዲሆንና ማንኛውንም መልካም ሥራ ለመሥራት ብቁ እንዲሆን ነው፡፡
በዚህ መሠረት የቅዱሳት መጻሕፍት ደራስያን ሁለት ሁለት ናቸው፤ አንድኛው የሃይማኖትን ሂደት የሚመራው መንፈስ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፣ ሁለተኛው የእያንዳንዱ መጽሐፍ አዘጋጅ ራሱ ደራሲው፡፡ ለሁለቱም ድርሻ ድርሻ አላቸው፤ መንፈስ ቅዱስ በስውር በደራሲው መንፈስ አድሮ ይመራል፤ ደራሲው ደግሞ ብራና ፍቆ፣ ዳምጦ፣ ቀለም በጥብጦ፣ የሚጽፍበትን ቋንቋ አጥንቶ፣ በተቻለ ዐቅም ተዘጋጅቶ ይቀርባል ፡፡ እንደዚህ ያለውን በፍጽም አእምሮው ያለውን ሰው መንፈስ እግዚአብሔር ይመራዋል እንጂ ዕፅ ፈርስ ጠጥቶ እንደ አበደ፡አብዶም እንደሚለፈልፍ አያስቀባጥረውም፤ወይም አብሾ ጠጥቶ እንደ ሰከረ አያስቀባጥረውም፤ ያለዚያም ዛር እንደ ያዘው አያስጎራውም፡፡

Friday, June 29, 2012

ለምን አልሰለምሁም? ክፍል ሁለት ምሥጢረ ሥጋዌ


ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ በሰፊው ለክርስቲያን በብዙ ቦታዎች ተጽፎል፡፡ 
ለነዲዳትና ለመሰሎቹ በመልስና በመረጃ መልክ ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ በአጭሩ ተገልጧል፡፡ 

እሱም በመጀመሪያ የኦሪትን ከዚያ የቁርአንን ስለአዳም መውደቅ ታሪክ መነሻ አድርጎ ታትቷል፡፡
(ዘፍ 2፡7) ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ከመሬት አፈር ወስዶ፣ ሰውን ከአፈር አበጀው፣ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስ እፍ አለበት፡፡ ሰውም ሕይወት ያለው ፍጡር ሆነ፡፡
(ዘፍ 2፡15)ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ሰውን በኤደን የአትክልት ቦታ አኖረው፤ይህንም ያደረገው ሰው የአትክልቱን ቦታ እንዲያለማውና እንዲኩተኩተው ነው፤ እግዚአብሔር አምላክ ሰውን በአትክልቱ ቦታ ከሚገኙት ዛፎች ሁሉ ፍሬ ብላ፤ ነገር ግን ደጉን ከክፉ ለመለየት የሚያስችል ዕውቀት ከሚሰጠው ዛፍ ፍሬ አትብ፤ ምክንያቱም ከዚህ ፍሬ በበላህበት ቀን በርግጥ ትሞታለህ ብሎ አዘዘው፡፡
(ዘፍ 2፡18) እግዚአብሔር አምላክም አለ፤ ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም፡፡ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት፡፡
(ዘፍ 2፡20) ----- ፤ እግዚአብሔር አምላክም በአዳም ከባድ እንቅለፍን ጣለበት አንቀላፋም፣ ከጎድኑም አንዲት አጥንት ወስዶ ስፍራውን በሥጋ ሞላው፤ እግዚአብሔር አምላክም ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት፤ ወደ አዳምም አመጣት፣ አዳምም ይህች አጥንት ካጥንቴ፣ ሥጋም ከሥጋዬ ናት እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል፡፡ ስለዚህ ሰው አባትና እናቱን ይተዋል፣ ከምሽቱም ይጣበቃል፤ ሁሉም አንድ ሥጋ ይሆናሉ፡፡ አዳምና ምሽቱ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ፡፡ አይተፋፈሩምም ነበር፡፡
(ዘፍ.3፡1……፣)አዳምና ሔዋንም በዚህ ሁኔታ በገነት መካከል የፍጥረታት ሁሉ ገዥዎች ሁነው ሲኖሩ ሰይጣን ቀናና በእባብ ተመስሎ የተከለከለችውን ዕፅ እንዲበሉ በማድረጉ የአምላካቸውን ትእዛዝ በመተላለፋቸው ተረግመው ከገነት ወጡ፡፡ 
ይህ ታሪክ በቁርአን ደግሞ እንዲህ ነው፤ (ላሟ ምዕራፍ ፡2፡34-38) መላእክትንም ለአዳም ስገዱ ባልነ ጊዜ ከዲያብሎስ በቀር ሁሉም ስገዱ፣ እሱ ግን እምቢ አለ፣ ኮራም በዚህም ከከሐዲዎች ተቆጠረ አዳም ሆይ !አንተ ከነምሽትህ በገነት ተቀመጥ፤ ከርሷም በፈለጋችሁት ስፍራ በሰፊው ተመገቡ፣ ግን ይህችን ዛፍ አትቅረቡ፤ ከበደለኞች ትሆናላችሁና አልነም፡፡ ከርሷም ሰይጣን አዳልጦ (አሳስቶ) በውስጡ ከነበሩበት ድሎት አወጣቸው፡፡ አንዱ ለሌላው ጠላት ሁናችሁ ውረዱ፣ ለእናተም በምድር ላይ እስከ ጊዜያችሁ ድረስ መጠለያና ሥንቅ አለላችሁ፡፡ በኦሪትም ሆነ በቁርአን እግዚአብሔር ትእዛዙ በመጣሱ አዝኖ አዳምና ሔዋንን ከገነት እንዳስወጣቸው ቁልጭ ተደርጎ ተጽፏል፡፡ ቁርአን ከዚህ በኋላ ስለመታረቅና ድኅነት የሚናገረው የለም፣ ከአሕዛብ ልማድ ከመጣው መሥዋዕተ እንስሳ በቀር፡፡ ኦሪትና ወንጌል ግን በትንቢትና በፍጻሜ አምላክ ዓለምን የታረቀው በልጁ ደም መሆኑን አብራርተው፣ ነግረው ደምድመዋል እዳም የፈጣሪውን ትእዛዝ በመተላለፍ ከገነት ወጥቶ፣ እሱ ብቻ ሳይሆን በመላ ዘሩም በምድረ ፋይድ ሲኖር በሦስት አካላት ሲመሰገን የሚኖር እግዚአብሔር በዳዩን አዳምን ይቅር ለማለት ወሰነ፡፡(ዘፍ.3፡1-4) ለዚህም መታረቂያ መሥዋዕት አስፈለገ፡፡ በደሉም ግዙፍ ስለሆነ ለመሥዋዕቱ የሰውና የእንሰሳ ደም የማይበቃ ሆነ፡፡ የስላሙ የመሐመዱ፣ የቁርአኑ አምላክ ቢሆን ኑሮ ያፍርድ እንደ ዐጤ ስለሚሰራ ምሬሃለሁ ቢል ይበቃ ነበር፡፡ የአብርሃም አምላክ ግን እውነተኛ ዳኛም መሓሪም ስለሆነ፣ ተቀዳሚና ተከታይ የሌለው ልጁ ሥጋ ለብሶ እንዲሠዋ ወሰነና ላከው፡፡ (ዘፍ.3፡15) በአንተና በሴቲቱ መካከል፣ በዘርህና በዘርዋ መካከል  ጠላትነትን አኖራለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል አንተም ሰኮናውን ትቀጠቅጣለህ ባለው መሠረት፣ በዳይም ተበዳይም ልጅ ልጃቸውን አዋጡና የአምላክ ልጅ እግዚአብሔር ወልድ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ፣ሥጋ ለብሶ፣ ትስብአርትን ተዋሕዶ የሰውን ልጅ ጠላት ሰይጣንን ድል ነሥቶ ፣ ከዲያብሎስ ባርነት ከሲኦልና ከገሃነም ሥቃይና ኩነኔ አዳነ፡፡ የተበዳይና የበዳይ ልጅ (ዘር) በተዋሕዶ ሥጋ ተሰቅሎ ዓለምን አዳነ፡፡ ከሦስቱ ሥላሴ፣ ከሠለስቱ አካላት አንዱ በተለየ አካሉ እግዚአብሔር ወልድ ሥጋ ለብሶ፣ ተሠቃይቶ፣ ተገፎ፣ ተገርፎ፣ ተሰቅሎ ዓለምን እንዲያድንና ከአባቱም ከራሱም ከመንፈስ ቅዱስም ጋራ እንደያስታርቅ እንዴት እንደ ተወሰነ በሥሉስነት ሲመሰገን ከሚኖረው ከገናናውና ከረቂቁ አምላክ አንዱ እግዚአብሔር በቀር ማንም አያውቅ፡፡ ተበዳዩ አምላክ በዳዩን ሰውን ይቅር የሚልበት ጊዜ ሲደርስ፣ በመበሠሩ በቅዱስ ገብርኤል አማካይነት፣ የቅድስት ድንግል ማርያምን ይሁን ይደረግልኝ ፈቃድ ብኋላ፣ አንድያ፣ ተቀዳሚ፣ ተከታይ የሌለው ልጁን ሥጋ እንዲዋሃድ እንዲለብስ ወደ ቅድስት ድንግል ማርያም ላከ፡፡

በልደት ሦስቱም፤ አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ተስማምተዋል፣ ተባብረዋል፡፡ አብ መርጧል፣አጽንቷል፤ መንፈስ ቅዱስ በላያዋ ላይ አድሮ ወላዲተ አምላክ ማኅደረ መለኮት እንድትሆን አመቻችቷል፣ አዘጋጅቷታል፡፡ እግዚአብሔር ወልድም ከነፍሷ ነፍስ ከሥጋዋ ሥጋ ነሥቶ ፍጹም ሰው ሁኗል፡፡ ስለዚህም በአንድ አካል የተዋሐደ ሰውና አምላክ ይባላል፡፡ ስለዚህም በአንድ እረኛ አንድ መንጋ በተሰጠው ውሳኔ አንድ መለትስ ይባላል፤ (መለትስም ሰውና አምላክ ወይም መለኮትና  ትሰብእት ማለት ነው) በመለኮቱ የአብ ልጅ፣ በትስብእቱ (ሥጋው) የማርያም ልጅ ይሉሃል ይህ ነው፡፡ በግዕዙም ወልደ አብ በመለኮቱ ወልደ ማርያም በትስብእቱ ይላል ውሳኔው፡፡ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆነ የሚያሰኘውም ይህ ነው፡፡ በመለኮቱ አምላክ አማልክት፣ ፈጣሬ ዓለማት ሲሆን፣ በትስብእቱ ደግሞ ንጉሠ ነገሥት፣ ሊቀ ካህናት፣ ሊቀ ሰማዕት፣ ሊቀ ነቢያት ነው፡፡ እንደ ሰውነቱ፣ ሰው መሆኑን ለማጠየቅ ትንሽ በትንሽ አድጓል፣ እንደ ሕፃናት አልቅሷል፣ደክሟል፣ ተርቧል፣ ተጠምቷል፣ ምራቅ፣ ደም ወጥቶታል፣ ሙቷል፡፡ አምላክ እንደ መሆኑ፣ አምክነቱን ለማጠየቅ (ለማስረዳት) በድንግልና ተወልዷል፣ በተዘጋ ቤት ገብቷል፣ በባሕር ላይ ያለ ጀልባ ሂዷል፤ ከሞተና ከተቀበረ በኋላ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ተነሥቷል፤ በዚህም አንደ መለትስነቱን እነረዳለን፡፡መለትስ መሆኑን ያልተረዱ ብዙ ሰዎች ትስብእትን ሲያይ የተነገሩትን ቃላት፣ ጥቅሶች፣ ዐረፍተ ነገሮች፣ ባነበቡ ቁጥር ለማረም ወይንም ለማጣመም ይሞክራሉ፡፡ ይህ ግን ካለማወቅ የመጣ ነው፤ ልኩ መለኮቱነ ሲያዩ የተነገሩትን ለመለኮቱ ሰጥቶ በመለኮት ባሕርይ መተርጎም፣ በትስብእት፣ ለትስብእት የተነገሩትን ደግሞ ለትስብእት ሰጥቶ ከነበቡ በኋላ አንድ  አካል አንድ መለትስ ብሎ አስታርቆ አስማምቶ መፍታት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ወልድ የአብና የማርያም ልጅ፣ በአንድ መለትስ መሆኑን ለመረዳት በሰፊው የሚፈልግ ሁሉ ወደ ፊት በሌሎች ክፍሎች የምናየው ይሆናል፡፡ ከዚህ ግን ፍጽም አምላክ እና ፍጹም ሰው በአንድ አካል እንድመለትስ መሆኑን ለማስረዳት የሚከተሉት ተጠቅሰዋል፤ (ዮሐ.1፡1-14) 3፡1618፤ መዝ.2፡68፤ 109፡4፤ ሉቃ.23፡34፤ ዮሐ.10፡30፤14፡6፤20፡17፤ ኢሳ.61፡13፤ ሉቃ.418-19፤53፡11-12፤ ዮሐ.14፡28፤31፤ መዝ. 21፡1፤ ማቴ.27፡46፤ ሉቃ.13፡32፤ 2ቆሮ.1፡3፤11፡31፤ ኤፌ.1 ኢሳ.3፤17፤ ፊል.2፡6፣10፤ 1ጴጥ.1፡3፤ 2ጴጥ 1፡17-18፤ ግብ.ሐዋ 2፡24፤ ራእ.1፡6፤3፡12 ዮሐ.6፡37-39፤7፡29፤ 1፡36፤8፡42፤9፡4፤ ሉቃ.4፡43፤ ገላ.4፡4፤ ዮሐ.4፡9) ከቅዱሳት መጻሕፍት አምላክና ሰው መሆኑን ለመግለጥ የተጻፈ ለቁጥር የሚዳግቱ ብዙ ጥቅሶች አሉ፡፡ቁርአንም የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ያምናል፤ ይህንም

Monday, June 25, 2012

ለምን አልሰለምሁም? ክፍል አንድ ምስጢረ ሥላሴ


ኢየሱስ ክርስቶስ ምስጢረ ሥላሴን አላስተማረም፣ የአምላክ ልጅም አይደለም፣ አምላክ ልጅ ነኝም አላለም እያሉ ዓለምን ለሚያወናብዱት ለነአሕመድ ዲዳት ማብራሪያ  

ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በአካል አንድ ብቻ አልነበረም፡፡ በአካል በስም፣ በግብር ሦስት፣ በመለኮት፣ በባሕርይ በህልውና አንድ ሁኖ አንድ አምላክ እየተባለ ዘለዓለም ሲቀደስ ኑሯል፤ይኖራል፡፡
ሥላሴ በስም:- አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይባላሉ፡፡ በግብር አብ ይወልዳል፤ ያሠርጻል፤ ወልድ፤  ይወለዳል፤ መንፈስ ቅዱስ ይሠርጻል፡፡ በአካል አብም፤ ፍጹም አካል (ህልውና፤ ገጽ) አለው፤ እንደዚሁም ወልድና መንፈስ ቅዱስ ከአብ የተለየ ፍፁም አካላት አሏቸው። አካልና ሰውነትን  ያልተማሩ ሰዎች ያደባልቋቸዋል፤ አካል ሦስቱም፣አብ ወልድ ፡ መንፈስ ቅዱስ ለእየራሳቸው አሏቸው ሰውነት ግን የሚጨበጥ የሚዳሰስ ያለው ወልድ ብቻ ነው፡፡ ይኽውም ሥጋ በመልበሱ፡፡ በምስጢረ ሥላሴ አካል ለቀዋሚ ነገር ለመንፈስ ነው የሚነገረው፤ አይታይም አይዳሰስም፤ መንፈስ ነው፡፡ አካል በምናውቃቸው በሌሎቹ ቋንቋዎች (ፕሮሶፓን ግሪክ፤ ፔርሶና ላቲን፤ ፔርሶን እንግሊዝ፣ ጣልያን ፈረንሳይ ነው፡፡ ሰውነት (በአልካ በሚዳሰስ ትርጉሙ)ሶማ ግሪክ፣ ቦዲእንገሊዘ፡ ኮርም ጣልያን፡ በፈረንሳይ በንባብ ኮር በአፃፃፍ ኮርጥስ፡ ላቲን ኮርፑስ ነው፡፡ ስለዚህ ነው ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ በተለየ ረቂቅ አካሉ ሥጋ ስለለበሰ። ሰውነት(የሚዳሰስ አካል) አለው የሚባለው፡፡ ባሕሪያቸው መለኮታቸው፣ መንግሥታቸው፣ ሥልጣናቸው ግን አንድ ነው፡፡ በአካል ሦስት ስለሆኑና በመለኮት፣ በባሕርይ አንድ ስለሆኑ፣ እኔ እያለ በነቢያት በክርስቶስ፣ በሐዋርያት፣ እግዚአብሔር ሲያናግር ኑሯል፡፡  
  1.  (ዮሐ. 1፡1-3) በመጀመሪያ ቃል ነበረ፤ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፡፡ ይህ በመጀመሪያ በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ፡፡ ሁሉም በእሱ ሆነ፡፡ ከሆነውም አንዳች ስንኳ ያለ እርሱ የሆነ የለም። ከዚህ ላይ ከመጀመሪያ ጀምሮ ከእግዚአብሔር አብ ጋራ ሌላ እግዚአብሔር ወልድ እንዳለ እና ያለእሱም ምንም  እንዳልሆነ ይናገራል፤ በአካል የተለያዩ በመለኮት ግን አንድ የሆኑ፤ ሁለት አካላት፤ አንድ እግዚአብሔር እንድ እግዚአብሔር እንዳለ  ወንጌላዊው ቁልጭ አድርጎ ገልጧል፤ ከዚህ ላይ የተጠቀሱት ሁለቱ አካላት አብና ወልድ ናቸው፣ ዝቅ ስንል ደግሞ ሦስት አካላት መሆናቸውን እናያለን፡፡ 
  2.    (ማቴ.3፡16-17) ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኋ ወጣ፤ እነሆም ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ወርዶ ከእሱ ላይ ሲቀመጥ አየ፡፡ እነሆም ድምፅ ከሰማይት ወጥቶ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ፡፡ በዚህም በአምሰላ ርግብ  የወረደው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፤ የምወደው ልጄ ያለ እግዚአብሔር አብ ፤ ተጠማቂው ሰው የሆነው እግዚአብሔር ወልድ በትስብእቱ ዐማኑኤል፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የተባለው፣በኋላ የቤተክርስቲያ ሊቃውንት ሥላሴ ብለው የሰየሟቸው አካላት፣ አብ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ መሆናቸውን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡(ማር.1፡911፤ ሉቃ.3፡21-22) 
  3.   ይኽው ታሪክ በድብረ ታቦርም ተደግሟል፣ ያውም ከትእዛዝ ጋራ፣ (ማቴ.17፡1-6፤ማር.9፡2-13 ሉቃ.9.28-36)"እነሆም ከደመናው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት፡፡"፥ 
  4.  (ዮሐ.11፡4) ኢየሱስም ሰምቶ፣ ይህ ሕመም የእግዚአብሔር ልጅ በእርሱ ይከብር ዘንድ ስለ እግዚአብሔር ክብር ነው እንጂ ለሞት አይደለም አለ፡፡ 
  5.    (ዮሐ.11፡-፡27) አዎ!ጌታ ሆይ አንተ ወደ ዓለም የሚመጣው ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆንህ እኔ አምናለሁ አለችው፡፡ በዚህ ጊዜ ቁርአንና እስላሞች እንደሚሉት አምላክ ባይሆን ኑሮ፣ አይደለሁም  ተሳስተሸል፣ እኔ አምላክ አይደለሁም ይላት ነበር፡፡ 

Wednesday, June 6, 2012

በደብረ ይድራስ ቅ/ጊዮርጊስ ተቃዋሚዎችን ለመበተን የተሰማራው ፖሊስ አስለቃሽ ጢስ ይዞ ቤተ መቅደስ ገባ

  • በአስለቃሽ ጢሱ ጸሎተ ቅዳሴው ታጉሏል፤ ሕፃናት፣ ምእመናንና አገልጋዮች ታፍነዋል:: 
  • ለውዝግቡ መፍትሔ ያፈላልጋል የተባለ ጥምር ኮሚቴ ተቋቁሟል:: 
  • ከ70 - 80 የሚደርሱ የደብሩ ሠራተኞችና ምእመናን እንደታሰሩ ናቸው::
  • ከንቲባ ኩማ ደመቅሳ ሊቀ ጳጳሱን በስልክ አነጋግረዋል::

 በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ በሚገኘው ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከይዞታ ማስከበር ጋራ በተያያዘ ትናንት፣ ግንቦት 27 ቀን 2004 ዓ.ም ጠዋት በአጥቢያው ምእመናን መካከል ግጭት ተቀስቅሷል፤ በግጭቱ የአንድ ፖሊስ ሕይወት አልፏል፤ ስድስት ፖሊሶችና በርካታ ምእመናንም ተጎድተዋል፤ ብዙዎቹን የደብሩ ሰበካ ጉባኤ አባላትንና ሌሎች ሠራተኞችን ጨምሮ በቁጥር ከ70 - 80 የሚሆኑ የአጥቢያው ወጣት እና አዛውንት ምእመናን ከየመንደሩ በፌዴራል ፖሊስ አባላት እየተሰበሰቡ መታሰራቸው ነው የተነገረው፡፡