Friday, December 7, 2012

♥አባ ሊቃኖስ ዘእምተሰዓቱ ቅዱሳን♥



በስመ ሥላሴ
ወበዛቲ ዕለት አዕረፈ አባ ሊቃኖስ ዘእምተሰዓቱ ቅዱሳን
“ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅመ እግዚአብሔር”(“የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።”) መዝ.፻፲፭፡፲፭ (115፡15)
“እኛስ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ዝም ማለት አንችልም” ሐዋ.፬፡፳ (4፡20)
የቅዱሳን ሕይወት ተርታ ታሪክ ወይም ተረት አይደለም ይልቁንስ እግዚአብሔርን የሚከተሉና በሥራቸው ሁሉም የእርሱ ጥበቃ ያልተለያቸው ሰዎች ታሪክ ነው። (ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ)
 የተሰዓቱ ቅዱሳን ሐዋርያዊ ተልእኮ መቅድም
ተሰዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ የመጡት አልአሜዳ በነገሰ በአምስት ዓመት ነው።
 እንደመጡት እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነው በአክሱም ዐስራ ሁለት ዓመት ኖረዋል።
ተሰዓቱ ቅዱሳን በስም አባ አሌፍ፣ አባ አረጋዊ፣ አባ ጰንጠሌዎን፣ አባ ገሪማ፣ አባ ጵሕማ፣ አባ አፍጴ፣ አባ ሊቃኖስ፣ አባ ይምዓታ፣ አባ ጉባ ይባላሉ። እኚ አባቶች ወደ ኢትዮጵያ እንደገቡ ዝም ብሎ አልተቀመጡም፤ ለሥራቸው በር ከፋች የሆነውን ቋንቋ፣ የሕዝቡን ባህል ጠንቅቀው ካወቁ በኋላ ላይ በአንድ አከባቢ ከመኖር ይልቅ መንፈስ ቅዱስ በመደባቸው ቀጥታ ማስተማርን መርጠው መንፈሳዊ ዓላማቸውን ለማሳካት የአክሱምን ነገስታት እርዳታና ድጋፍ አልተለያቸውም ነበር። እኚው ተሰዓቱ ቅዱሳን የመጡበት ሀገራት ሮም፣ እስያ፣ አንጾኪያ፣ ቁስጥንጥንያ፣ ቂሳርያ፣ ኪልቂያ ሲሆን በነበሩበት ጊዜያትም፡-
. ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን አጽንቶልናል።
. መጽሐፍትን ተርጉሞልናል።
. ስብከተ ወንጌልን አስፋፍተዋል።
. ብዙ ገዳማትን መስርተዋል።
. ሥርዓተ ምንኩስናን አደራጅተዋል።
 ስለ እነዚህ ቅዱሳን ይህችን ታህል ካልኩኝ በዛሬው የዕረፍት በዓላቸው የሚታሰበው ከእነዚሁ ቅዱሳን አንዱ ስለሆኑ  ስለ አባ ሊቃኖስ ትንሽ ልበላችሁ።

Wednesday, December 5, 2012

ክብረ ቅዱሳን



በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
የቀበና ምስራቀ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤ/ክ የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መምህር እና የሰብከተ ወንጌል ኃላፊ
ክፍል አንድ 

ክፍል ሁለት 
 

የቅድስት ቤተክርስቲያን አባቶች የእርቀ ሰላም ጉባኤ በዳላስ ቴክሳስ ተጀመረ

ምንጭ ፡-
“ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተ ክርስቲያን - ስለ ቤተ ክርስቲያን ሰላም ጸልዩ”።


አባቶች በጋራ ከጉባኤው በፊት በተገናኙበት ወቅት
በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በርካታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኞች ካህናት አባቶች፣ ዲያቆናት፣ ምዕመናን እና ምዕመናት በጉጉት ሲጠብቁት የነበሩት የቅድስት ቤተክርስቲያን አባቶች የእርቀ ሰላም ጉባኤ ትላንት ረፋዱ ላይ በዳላስ ቴክሳስ በሚገኘው ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በጸሎት ተጀምሮ በመቀጠል በአካባቢው በሚገኘው ሆቴል የድርድሩ እና ለቅድስት ቤተክርስቲያን ሰላምን ለማምጣት በአባቶቻችን እና በምዕመናን ጸሎት እና ልመና የተሳካ እንደሚሆን የሁሉም ወገኖች እምነት ነው።

Tuesday, December 4, 2012

ታላቅ መንፈሣዊ ጉባኤ December 15 & 16, 2012

ትላንት ዋልድባ ታረሰ፣ ዛሬ የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ሊፈርስ ነው፣ ነገስ . . . በተመሳሳይ ርዕሶችና በእርቀ ሰላሙ ዙሪያ ውይይቶች ተዘጋጅተዋል እንዳያመልጦት!

ዓለምዓቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች አንድነት፣ ቀድሞ ዋልድባን ለመታደግ የተቋቋመው ኮሜቴ ለአራተኛ ጊዜ በወቅታዊ የቤተክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ለመነጋገር እና የመፍትሄ ሃሳቦችን ለመጠቆም ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ ባለሙያዎችን ጋብዞ ለመነጋገር የሁለት ቀናት ተከታታይ ጉባኤ አዘጋጅቷል። የእርሶ ተሳትፎ እየት ድረስ ነው? ለቤተክርስቲያንዎ ሊያበረክቱ የሚችሉትን ለመጠቆም ተዘጋጅተናል፣ ኑ! እንምከር ቤተክርስቲያንን ለተተኪው ትውልድ ከነሙሉ ክብሯ ለማስተላለፍ አብረን እንስራ!
እግዚአብሔር አምላክ ቤተክርስቲያናችንን በረደኤት ይጠብቅልን አሜን

ቅዳሜ Dec. 15, 2012 እሑድ DEC. 16, 2012
St. Andrew UMC ርዕሰ አድባራት ደብረ ሰላም ቅ/ማርያም ቤ/ክርስቲያን
845 N. Haward Street 1360 Buchanan Street, NW.
Alexandria, VA 22304 Washington, DC 20018
2:00 – 6:30 pm. 4:00 – 8:00 pm