Thursday, November 24, 2011

የአብነት ት/ቤቶችና ገዳማት በኢትዮጵያ

ቤተ ክርስቲያን ሰማይና ምድር ከመፈጠራቸው በፊት ነበረች። ዓለማት ከተፈጠሩ በኋላ በዓለመ መላእክት፣ በዓለመ መሬት በሕገ ልቡና እና በሕገ ኦሪት እግዚአብሔር በመረጣቸው ነቢያትና ካህናቱ አማካኝነት ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር ስታገናኝ ኖራለች። በዘመነ ሐዲስ ደግሞ በደመ ክርስቶስ ተዋጅታ ሕገ ወንጌልን ስትናኝ እና አምልኮተ እግዚአብሔርን ስታስፋፋ ኖራለች። በእነዚህ አዝማናት ሁሉ ስለ እርሷ ሳይፈሩና ሳያፍሩ አንገታቸውን ለሰይፍ፣ ጀርባቸውን ለግርፋት፣ እግራቸውን ለሰንሰለት የሰጡላት፣ በብዙ መከራዎች የተጋደሉላትን አበው፣ ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ሰማዕታትን እና በእነርሱ መንገድ የተጓዙ ብዙ ሊቃውንትን አፍርታለች (ዕብ ፲፩)
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሕገ አበውን፣ ሕገ ኦሪትንና ሕገ ወንጌልን አስተባብራ በመያዝ የጥበብ ምንጭ፣ የሥርዓት መፍለቂያ፣ የዕውቀት ባሕር ሆና ሁሉ የተሟላላት ስንድ እመቤት ናት። በማኅበራዊ አገልግሎቷ ደግሞ የድኩማን መጠጊያ፣ ያዘኑና የተከፉ መጽናኛ፣ የማንነትም አሻራ ነች። ለዚህም የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በተለያዩ ገዳማት፣ አድባራት፣ አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ የአብነት /ቤቶች ተቀዳሚ ተጠቃሾች ናቸው። በተለያዩ ጊዜያት የተንኮልና የክህደት ቋጠሮ ይዘው የመጡ መስሐቲያን (አሳሳቾች) አፍረው የተመለሱት ከአብነት /ቤቶቹ በወጡ መምህራን ነው። ከዚህም በተጨማሪ ለሀገር መሪ ለሕዝብ አስተማሪ በመሆን ሕዝብን ያገለገሉ ደጋጎች ከእነዚህ የአብነት /ቤቶች በአጠቃላይ ከቤተ ክርስቲያን የወጡ ናቸው።
ሌላው ልንገነዘበው የሚገባ ቁም ነገር ቢኖር ገና ያልደረስንባቸው ብዙ እምቅ መንፈሳዊ ሃብቶች ያሉን መሆናቸዉ ነው። ለምሳሌም፦ በዜማዉ የአጫብር፣ የቆሜ፤ በቅኔው የዋድላ፣ የጎንጅ፤ በመጻሕፍት ትርጓሜ የላይ ቤት፣ የታች ቤት እየተባሉ የሚሰጡ ትምህርቶች ይትበሃሎች አሉን። እነዚህ መሠረታቸው የቤተ ክርስቲያን ትምህርትና ሥርዓት ሆነው አካባቢያዊ መልክ ያላቸውን እምቅ እሴቶች ልንፈለፍላቸውና ልንንከባከባቸው የሚገቡ ናቸው።
የቤተ ክርስቲያኒቱ አብነት /ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አሁን በዓለም እውቅ ከሆኑት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንዱ ከሆነው ከሐርቨርድ ዩኒቨርሲቲ ሥርዓተ ትምህርት ጋር የሚያመሳስለው ነገር ያለው ሲሆን ይህም አግራሞትን የሚፈጥርና የሥረዓተ ትምህርቱን ጥንካሬ የሚያሳይ ነው። ሆኖም የቤተ ክርስቲያኒቱን ሥረዓተ ትምህርት በዘመን ቀዳማዊ ሆኖ መገኘቱ እጅግ የሚያኮራ ነው።
የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ ሳይከለስና ሳይበረዝ ተጠብቆ እስከአሁን እንዲዘልቅ ያደረጉት ገዳማት፣ አድባራት፣ አብያተ ክርስቲያናት እና የአብነት /ቤቶች ናቸው። ስለሆነም እነዚህ የትምህርት ማዕከላት በተለያዩ ችግሮች ምክንያት እንዳይዘጉ፤ መምህራኑና ተማሪዎቻቸው እንዳይሰደዱ፣ ወንበር እንዳይታጠፍ በጋር እና በተናጠል ድጋፍ ሲደረግ መቆየቱ የሚታወቅ ነው። ሆኖም ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ በመምጣቱ የእሳት ማጥፋቱ ሥራ በልማት ቢታገዝና ዘላቂ መፍትሔ ማግኘት ቢቻል መልካም መሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ እና በምእመናን ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ ጉዳይ ነው።    
ገዳማት አድባራትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና ለኢትዮጵያ ተቆጥሮና ተሰፍሮ የማያልቅ ውለታ የዋሉ፤ እንደ ዓይናችን ብሌን ልንጠብቃቸው የሚያስፈልጉ የተቀደሱ ሥፍራዎቻችን ናቸው፡፡
እነዚህ ገዳማት፣ አድባራትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ቤተ ክርስቲያኒቱን የሚመሩ የሊቃነ ጳጳሳቱ መገኛ፣ እና በአፍ በመጣፍ የመጣን አጽራረ ቤተ ክርስቲያን የሚመልሱ የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን መፍለቂያ ናቸው፡፡ ገዳማቱ ስለሀገር፣ ስለወገን የሚጸልዩ ከእነርሱም አልፎ ለሌላው መዳን ምክንያት የሚሆኑ መናንያን፣ መነኮሳት መኖሪያ፣ የምእመናን ተስፋ፣ በረከት ማግኝያም ናቸው፡፡

ገዳማቱ፣ አድባራቱና የአብነት ትምህርት ቤቶቹ ለኢትዮጵያ የሥነ ጽሑፍ፣ የሥነ-ሥዕል፣ የፊደል፣ የሥነ-ሕንጻ ምንጭነትና አጠቃላይ የሥልጣኔና የትምህርት ማዕከል በመሆን ያገለገሉና እያገለገሉ ያሉ የሀገር ኩራት ናቸው፡፡

በውስጣቸው የሚገኙት ንዋያተ ቅድሳት፣ ሥነ-ሕንጻዎችና ቅርሶች ለሀገርና ለወገን ኩራት ከመሆን አልፈው ዓለም አቀፍ ቅርሶች እስከ መሆንና ለሀገሪቱም በቱሪዝሙ ዘርፍ ከፍተኛ ገቢ እያስገኙ ያሉ ውድ ሀብቶቻችን ናቸው፡፡

እነዚህ የቤተ ክርስቲያን፣ የሀገር፣ የምእመናን ተስፋና ኩራት እንዲሁም የማንነታችንና የታሪካችን መነሻ የሆኑት ገዳማት፣ አድባራትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ዛሬ ተገቢው ትኩረት ባለማግኘታቸውና በበቂ ሁኔታ አስታዋሽ በማጣታቸው ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል፡፡

ገዳማቱ ሁሉ ካለባቸው ችግር ተላቀው በቋሚነት ራሳቸውን በልማት እንዲችሉ ለማድረግ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሁሉንም ምእመናን ተሳትፎ የሚጠይቅ ሰፊ ሥራ ይጠብቃታል፡፡ ስለዚህ ወደፊትም ለውጥ እና የተጠናከረ እድገት እስኪመጣ ድረስ ደጋግመን ልናስብበት ይገባል፡፡

በመሆኑም በቀደሙት ቅዱሳን አባቶቻችንን ጽናትና ተጋድሎ ተጠብቀው የቆዩት ገዳማት፣ አድባራትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ዛሬ በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ችግሮች እየተፈተኑ ነው፡፡ መነኮሳቱ በረኀብና በዕርዛት እየተሰቃዩ ገዳማት እየተፈቱ ነው፡፡ የአብነት መምህራን በተማሪዎቻቸው ብዛት የደመቀ ሰፊ ጉባኤያቸው በምግብ እጦት የተማሪው ቁጥር እየተሸረሸረ፣ መምህራን ወንበራቸው እየታጠፈ ጉባኤውም እየተበተነ ነው፡፡

ከዕድሜ ዘመናቸው የተነሣ ጥንታውያኑ ቅርሶች እና የአብያተ ክርስቲያናቱ ሕንፃዎች እየፈራረሱ ነው፡፡ መጻሕፍትና ንዋያተ ቅድሳቱ ከአያያዝ ጉድለትም ሆነ በአግባቡ የሚጠቀምባቸው ጠፍቶ እየተጎሳቆሉ ነው፣ በተለይ በየገጠሩ በርቀት በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ከልብሰ ተክህኖ እስከ ዕለት መቀደሻ ጧፍ፣ እጣን፣ ዘቢብ እየጠፋ ቅዳሴ እየተስተጓጐለ ነው፡፡

እነዚህ ገዳማት፣ አድባራትና አብነት ትምህርት ቤቶች በአጽራረ ቤተ ክርስቲያን እና በዘራፊዎች ጭምር እየተዘመተባቸውም ነው፡፡ በየገዳማቱ ተመሳስለው በመግባት፣ በችግራቸው ሽፋን መነኮሳቱን በማሳሳት፣ በኣታቸውን ለቀው እንዲወጡ ለማድረግ ከመጣር አንሥቶ ጥንታውያኑን መጻሕፍትና ንዋያተ ቅድሳቱን እስከመዝረፍ ድረስ ብዙ ችግሮች እየተፈጸመባቸው ነው፡፡

በእነዚህ ገዳማት፣ አድባራትና አብነት /ቤቶች የሚገኙ አባቶችና አገልጋዮች ይህን ሁሉ ተደራራቢ መከራና ፈተናዎችን እየተጋፈጡ በእግዚአብሔር ቸርነት ጸንተው ቢቆዩም፤ ሃይማኖታዊ እሴቶችና ቅርሶቻችን ተጠብቀው ለትወልድ እንዲተላለፉ ለማድረግ በየጊዜው በተለያየ አቅጣጫና መንገድ ከየገዳማትና አድባራቱ እንዲሁም አብነት /ቤቶች የሚመጡትን የድረሱልን ጥሪ ተግባራዊ ምላሽ መስጠት የምእመናን ሃይማኖታዊ ግዴታ ነው፡፡

ለነዚህ ገዳማት፣ አድባራትና የአብነት ትምህርት ቤቶች መልስ መስጠት የቤተ ክርስቲያንን ተተኪ በብዛት ማፍራት ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያንን የሀገርን ታሪክና ቅርስ ማስጠበቅና መጠበቅም ነው፡፡ በተጨማሪም ከራሳቸው አልፎ ለቤተ ክርስቲያን፣ ለሀገር፣ ለወገንና ለዓለም ሰላም ቀን ከሌት የሚጸልዩትን መናኒያን ማትጋት ነው፡፡ ስለዚህም ይህንን የገዳማቱን የድረሱልን ጥሪ መስማት ያስፈልጋል፡፡

የሊቃውንትና አባቶች ካህናት መፍለቂያነታቸው እንዲቀጥል መናንያንና መነኮሳቱ ለቤተ ክርስቲያን፣ ለሀገርና ለወገን የሚጸልዩት ጸሎት እንዳይስተጓጐል፣ ጥንታውያኑ የብራና መጻሕፍት፣ ገድላትና ተአምራት ሌሎችም የእምነታችንና የማንነታችን መለያ የሆኑ ንዋያተ ቅድሳቱ በዘላቂነት ባሉበት እንዲጠበቁ ማድረግ ስፈልጋል፡፡

እሁንም የነዚህ ጥንታውያን ገዳማት፣ አድባራትንና የአብነት /ቤቶች ችግር የሰፋና በርካታ በመሆኑ የሁሉንም ዘርፈ ብዙ ተሳትፎ ይፈልጋል፡፡

በችግር ያሉትን ገዳማት፣ አድባራትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ጥሪ የማንን ፈጣንና ተግባራዊ ምላሽ እንደሚጠብቁ ለማወቅ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡

ገዳማቱን ከጠባቂነትና ከተረጂነት አላቆ ራሳቸውን በማስቻል መንገድ ቢቀናጅ ገዳማቱን፣ አድባራትና አብነት ትምህርት ቤቶቹን ከተመጽዋችነት ማላቀቅ ይቻላል፡፡

ቀጣይነት ያለው ልማት በጋራ መሥራቱና መተባበሩ ለነገ በይደር ይቆይ ሊባል የማይገባ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡

በመሆኑም ገዳማት፣ አድባራትና የአብነት ትምህርት ቤቶቹ ከተረጂነት ወጥተው ራሳቸውን በመቻል ታሪክ፣ ቅርስና የትምህርት ማዕከልነታቸው ተጠብቆ፤ በዘላቂነት እንዲቀጥሉ በማድረግ በኩል የሁላችንም አስተዋፅኦ አለ የማባል ነው ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የቤተ ክርስቲያን አካላት፣ ምእመናን ገዳማቱት አድባራቱ እንዲሁም የአብነት ትምህርት ቤቶች የሀገር ሀብት በመሆናቸው መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጭምር በጋራ መሥራት ይገባቸዋል፡፡

ለዛሬ የአራቱ መፃህፍተ፡ ጉባኤ፡ ትምህርት፡ ቤት፡ ጎንደር  በሚል እርዕስ የጎንደርን አብነት ት/ቤትን የሚሳ ቪሲዲ እንዲመለከቱ ተጋብዘዋል፡፡

Wednesday, November 23, 2011

የተቃውሞ ሰልፍ ጥቅምት 11 ቀን 2004 ዓ.ም. የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የተቃውሞ ሰልፍ እይታዎች ሙሉዉን ቪሲዲ


ጥቅምት 11 ቀን 2004 ዓ.ም. የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በአዲስ አበባ መንበረ ፓትርያሪክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተሐድሶ መናፍቃን ላይ ያደረጉትን የተቃውሞ ሰልፍ የሚያሳይ የ 20 ደቂቃ ቪሲዲ ለዛሬ አቅርበንላችኋል
በሰልፉ ላይ በአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት ከሚገኙ የ131 ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ያላቸውን የደንብ ልብስ(ዩኒፎርም)እና ነጠላ በመልበስ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምቱ ጉባዔው በተሐድሶ መናፍቃን ላይ እርምጃ እንዲወስድ ሲያሳስቡ ይታያል፡፡ ወጣት የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎቹ ተቃውሞአቸውን በአደባባይ ከማሰማታቸው በፊት ቀደም ባሉት ጊዜያት መዋቅራቸውን ጠብቀው ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤትና ጉዳዩ በቀጥታ ለሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን አካላት የተሐድሶ መናፍቃንን ማንነት የሚያጋልጥ ባለ 261 ገጽ የጽሑፍ ሰነድና 14 የምስል እና የድምጽ(VCD) ሰነድ በማስረጃነት ማቅረባቸው ቢታወቅም አደባባይ ለመውጣት እነዳላሰቡ ሆኖም ግን እነ በጋሻው፣ትዝታው፣አሰግድ፣ናትናኤል፣ያሬድና ሌሎችም የተሐድሶ ሎሌዎች ስማችን ጠፋ፣ መድረክ ተከለከልን፣ ተሐድሶ የሚባል የለም ፣ወዘተ….በማለት በለመዱት የግራ ዐይን የአዞ እንባቸው ሕዝቡን ለማሳሳት ሰልፍ እንወጣለን ብለው በማወጃቸው ምክንያት ወጥተው ተቃውሞአቸውን እንዳሰሙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ቪሲዲው፦
• “የዘማሪ” ትዝታው ሳሙኤልን መደብደብና መዋከብ ኋላም በድንጋጤ ጥግ ላይ ተደብቆ ጥርሱን እየነከሰ መንቀጥቀጥን፣
• የተሐድሶ መናፍቅ አሰግድ ሳህሉን ተንኮሳና መንቀዥቀዥ ኋላም መደንገጥና መሸማቀቅን፣
• የ“ዘማሪት” ቅድስት ምትኩንና “ዘማሪት” የትምወርቅን ድፍረትን፣
• የመናፍቁ ናትናኤል ታምራት በፍርሃት ታጥሮና ጥግ ይዞ መታየትን፣
• የ“መምህር” ተረፈን የመሃይም ድፍረትና በኋላም ቅሌትና ውርደት፣
• የሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴንና የቅ/ማርያም ገዳም አስተዳዳሪ አላዋቂነትና አድርባይነትን፣
• የአዲስ አበባን ሰንበት ት/ቤቶች በወኔ የታጀበ ጠንካራና የተደራጀ ተቃውሞን፣
• የቅዱስ ፓትርያርኩን ብስጭትና ወገንተኛነት፣
• የአዲስ አበባና የፌዴራል ፖሊሶችን የተረጋጋ፣ሕጋዊና ሰላማዊ የጸጥታ ማስተባበር ሥራን፣
• የአዲስ አበባ ምዕመናንን እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን ቅናት ወዘተ…..በአንጻሩ ደግሞ የተሐድሶ መናፍቃንን ድፍረትና አይን አውጣነት ያሳያል፡፡
• የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ቤተ ክርስቲያናችን በተሐድሶ መናፍቃን አትወረርም የሚል አገር አቀፍ ብሎም ዓለም አቀፍ የሆነ አጀንዳ ይዘው ታይተዋል፤
ቪሲዲው ከ“ዘማሪያኑ” እነ ትዝታው ሳሙኤል፣የትምወርቅ፣ቅድስት ምትኩ፣ምርትነሽ ጥላሁን፣ሃብታሙ ሽብሩ፣ሐዋዝ ተገኝ፣…..ከ“መምህራን” ናትናኤል ታምራት፣አሰግድ ሣህሉ፣ተረፈ፣ጋሻዬ መላኩ፣ስንታየሁ፣በፈቃዱ፣ታሪኩ አበራ….ነበሩበት፡፡የአዲስ አበባ ምዕመናን “ፍንዳታ”እያሉ የሚጠሯቸው የመነኩሴ ቆብ ያጠለቁ የተሐድሶ መነኮሳትም ነበሩበት፡፡
እነበጋሻውና ያሬድ አደመ ከመጋረጃው ጀርባ ሆነው ማስተባበርን መርጠዋል፡፡ማንነታቸው እንዳይታወቅ ፊታቸውን በሰፊ መነጽር ለመሸፈን የሞካክሩ ኮረዳዎችም በሰልፉ ነበሩበት
ቪሲዲው ኤዲት ስለሚጎድለውና ስለ ድምፁ ጥራትም ይቅርታ እንጠይቃለን። 
እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያናችንን ይጠብቅ አሜን።

Monday, November 21, 2011

እኔን ቀበሌ አላከኝም፣ የላከኝ ቅዱስ ሲኖዶስ ነው አቡነ ፋኑኤል


  • "እኔን ቀበሌ አላከኝም፣ የላከኝ ቅዱስ ሲኖዶስ ነው"
  • "14 ዓመት ደክሜ ከሰራሁት ቤቴ የትም አልወጣም"
  • "ወደዳችሁም ጠላችሁም ከዚህ የትም አልሄድም"
  • "አዎ አዲስ አበባ ላይ ቪላዎች ቤቶች አሉኝ፣ ያንን ትቼ ይህንን ህዝብ ላገለግል መጣሁ"
  • "ከዋሺንግተን ዲሲ እስከ ካሊፎርኒያ የኔ ግዛት ነው"
  • "ከዚህ በኃላ ስደተኛ፣ ገለልተኛ፣ መፃተኛ የሚባል ቤተ ክርስቲያን የለም"

የደብረ ምሕረት የትላንትናው ትዕይንት ይሄን ይመስል ነበር

በትላንትናው እለት በደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ላይ የተገኙት አቡነ ፋኑኤል በአዋሳ ላይ ልክ እንዳደረጉት ምንም የምታመጣው ነገር የለም የኔን የላከኝ ቀበሌ አይደለም ቅዱስ ሲኖዶስ ነው በማለት ለበዓል የታደመውን ምዕመን አስገርመውት ውለዋል። ትላንት በጠዋት የተጀመረው የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ከወትሮው በተለየ ሁኔታ የቤተ ክርስቲያኑ መግቢያ በፓሊስ ውጪው በተቃዋሚ ታውኮ ውሏል። ከሥርዓተ ቅዳሴው በኃላ በመምህር ዘላለም ወንድሙ አማካኝነት የማስፈራሪያ መልዕክት እንዲያስተላልፍ በተሰጠቅ ጥብቅ መመሪያ መሰረት መጥቶ በማያውቅበት የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አውደ ምህረት ላይ ቆሞ ባለሙዋልነቱን


 በሚገባ አረጋግጧል፣ እንደሚታወሰው መምህር ዘላለም ወንድሙ ከዚህ በፊት በቅዱስ ፓትሪያሪኩ ፈቃድ በአቡነ ፋኑኤል አደራጅነት እና አዋቃሪነት በተከፈተው  "የቤተ ክርስቲያን የውጪ ግንኙነት ጽ/ቤት" በሚባለው የሰሜን አሜሪካ የሰባኪያን እና ዘማሪያን ባለሙሉ ሥልጣን የበላይ ኃላፊ በሚል እንደተሾመ ይታወሳል። ለማንበብ እዚህ ይጫኑ በትላንትናው ድራማ ላይ አቡነ ፋኑኤል ለእኔ የሚናገርልኝ ሰው ከሌለ እኔው እራሴ ስለ እራሴ ማንነት እነግራችኃለው ብለው ህዝቡን ስለራሳቸው ግድል እና ድርሳን ሲናገሩ ከግማሽ ሰዓት በላይ አሳልፈዋል መዚህም መሠረት እኔ ልሰራ እንጂ ልከፋፍል አልመጣሁም ስለዚህ ከዚህ በኃላ ስደተኛ ወይም ገለልተኛ ሳንል በተጠራንበት በመሄድ እናገለግላለን በማለት አስጨብጭበዋል፣ እንደእውነቱ ከሆነ ቅዱስ ሲኖዶስ ከለየው ጋር ሄዶ መባረክም ሆነ እናቀራርባለን ብሎ ማለት ሥርዓት አልበኝነታቸውን የበለጠ ያጎላዋል እንጂ የሥራ ሰው መሆናቸውን አያስመሰክርም፡ ከዚህ በተጨማሪ "እኔ የሁሉም አባት ነኝ ማለታቸውም" ነገ የአባ ሰላማ ብሎግ ባለቤቶች (ፕሮቴስታንቶቹም) ቢጠሯቸው የሁሉም አባት ስለሆኑ ሄደው ሊባርኩ ነው ማለት ነው አንባቢ ያስተውል።


አቡነ ፋኑኤልና ካሕን መስሎ የቆመው body gourd
 የዛሬ 5 ዓመት ቅዱስ ሲኖዶስ መድቦኝ እዚህ መጥቼ ነበር፣ ነገር ግን  ሕዝቤብ በሀገሩ ማገልገል አለብኝ ከሚለው ጽኑ ፍላጎቴ የተነሳ ለቅዱስ ሲኖዶስ ደብዳቤ ጽፌ አዛውሩኝ በማለት ተዛውሬያለሁ ያሉት አቡነ ፋኑኤል አሁን ደግሞ ለ17 ዓመት ደግሜ በገዛ ገንዘቤ ያቋቋምኩትን ቤቴን እና  ሕዝብ ለገልግል ብዬ አዲስ አበባ ላይ ካሉት ቪላዎቼ እናንተን መርጬ ላገለግላችሁ መጥቻለው ብለዋል። ትላንት ከታዩት አስገራሚው ትዕይንት የህዝቡን ቀልብ የሳበው አባ ፋኑኤል ልክ እንደ ቅዱስ ፓትሪያሪኩ የግል ጠባቂ (body gourd) የካህን ልብስ አልብሰው ጥቁር መነጽሩን ደንቅሮ በተጠንቀቅ ሲጠብቅ እና የሙያውን ሥራ በሚገባ ሲወጣ ቆይቷል፣ የፓሊሱ ግርግር፣ ያቦዲ ጋርዱ ጥበቃ፣ የተቃዋሚዎች ስድብ በቤተ ክርስቲያናችን እስከ መቼ እንደሚቀጥል እና ታቦታችን ፊት እንዲህ አይነት ስድብ እና ውርደት መቀጠል እንደሌለበት የሁላችንም እመነት ቢሆንም አቡኑ ግን ወደዳችሁም ጠላችሁም ከሰራሁት ቤቴ ማንም አያስወጣኝም በማለት "ደርግ እንኳን ሁለት ያለውን አንዱን ነው የነጠቀው፣ እኔ ግን አንድ ስለሆነ ያለኝ እሱንም ስጥ የሚል ህግ የለም" ነበር ያሉት።


በእለቱ ከታዩት በርካታ ካሜራዎች እና ተቃዋሚዎች ጥቂቱ
 ሌላው አስገራሚው ትዕይንት ደግሞ አቡነ ፋኑኤል እስከ ዛሬ ድረስ እርሳቸውንም ጨምሮ በተለያየ ጊዜ የተለያዩ ሊቃነ ጳጳሳት በዋሽንግተን ዲሲ እና አካባቢው ተቀማጭ ሆነው ብዙ ሥራዎችንም የሰሩም ነበሩ የሞከሩም ደግሞ ነበሩ ነገር ግን አቡነ ፋኑኤል እርሳቸው የመጀመሪያው ለሥራ የመጡ የቅዱስ ሲኖዶስ ተወካይ እንደሆነ ሲናገሩ ምዕመናኑን ሁሉ አስገርመዋል፣ በተለያየ ጊዜ እየመጡ ያደራጇቸው የገለልተኛ አስተዳደር በሙሉ ምንም ነገር እንዳልተፈጠረ ነበር የተናገሩት በመቀጠልም ሁሉንም ይዘው ሥራ ለመስራት እንደተዘጋጁ እና ምዕመናኑንም ገንዘብ ያለህ በገንዘብህ ሙያ ያለህ በሙያህ ተባበረኝ ብለው ነበር የተናገሩት። እንደሚታወቀው የራሳቸውን ዝናና ክብር ሲወራ የሚወዱት አቡነ ፋኑኤል ትላንት የርሳቸውን ገድለ ፋኑኤል የሚያወራ ስለጠፋ "ስለ እኔ የሚናገር ከሌለ እኔው ስለራሴ ልናገር" ብለው ነበር እስቲ ስለ እኔ ገድል ተናገሩ ያሏቸው በሙሉ ለመናገር ባይደፍሩም ሕዝበ ክርስቲያኑን ከንቀታቸው የተነሳ ይሄንን ቤተ ክርስቲያን "ተቃዋሚዎች ጥይት ግዛ ብለው ሲሰጡኝ፣ እኔ ቤተ ክርስቲያን ገዛሁበት" "በመሆኑም አሁንም የእኔ ነው ወደፊትም የራሴው ነው" ነበር ያሉት ታዲያ እንዲህ አይነት "እኔነት" የተጠናወታቸው አባት እንዴት ነው ይህንን የተለያየ አላማ እና አካሄድ ያለውን ሕብረተሰብ እመራለሁ ብለው የተነሱት፣ ሲሆን እንደ ጥንት አባቶቻችን በትህትና እና በፍቅር መጀመር ሲገባቸው ገና ሲጀምሩ በትዕቢት እና በማናለብኝነት የጀመሩት አቡነ ፋኑኤል በአዋሳ ሕዝብ ላይ ያደረሱትን በደል በዋሽንግተን ሕዝብ ላይ እንደሚያደርጉት ይጠበቃል።

በዋሽንግተን አካባቢ በተለያዩ አስተዳደር ስር ያሉ አብያተ ክርስቲያናት አሉ ከነዚህም ጥቂቶቹ
፩/ በእናት ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር
፪/ በስተደኛው ሲኖዶስ አስተዳደር ያሉ
፫/ ያሉበገለልተኛ አስተዳደር ያሉ
፬/ ስደተኛውም ሲኖዶስ ወይም የሀገር ውስጥ ሲኖዶስ የማይመሩ ነገር ግን በራሳቸው የቦርድ አስተዳደር ያሉ
፭/ በእናት ቤተ ክርስቲያን ያሉ ነገር ግን ያፓትሪያሪኩን ስም በጸሎት የማይጠሩ
፮/ በገለልተኛ አስተዳደር ያሉ ነገር ግን የባለቤቶቻቸውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጥቂት አባላት ስር የሚተዳደሩ

እውነት ታዲያ አቡነ ፋኑኤልን መሪ አድርጎ ተቀብሎ የሚሰራ የትኛው ክፍል ነው እንደእርሳቸው አባባል የመጡት ለሁሉም ነው ብለዋል ታዲያ ይሳካላቸው ይሆን? ለጊዜው አሸንፈው የገቡት የራሴ ነው የግል ንብረቴ ነው ታክስ እከፍልበታለሁ ወይም መጦሪያ ቤቴ ነው በሚሉት ቤተ ክርስቲያን ብቻ ነው፣ ቀጥሎስ የትኛውን አሸንፈው ወይም ብልጣ ብልጥ አባባላቸውን ተጠቅመው ማስተዳደር ይችሉ ይሆን? ጥያቄውን ለአናባቢ በመተው የደፊቱን አብረን ለመመልከት የዛሬውን በዚህ እያጠቃለልን በመቀጠል የአቡነ ፋኑኤልን አካሄድ ለአንባቢ እየተከታተልን ለማቅረብ ቃል እንገባለን።

ኢትዮጵያ ሀገራችንን፣ ተዋሕዶ ሃይማኖታችንን ከአጽራረ ቤተክርስቲያን ይጠብቅልን አሜን


የመላው ዓለም የተዋሕዶ ቤተሰብ

ከሚካኤል በቀር የሚረዳኝ ማንም የለም። ዳን ፲፥፳፩


ቅዱስ ማለት ልዩ፥ ክቡር ማለት ነው፤ ሚካኤል ማለት ደግሞ «መኑ ከመ አምላክ፥ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው?» ማለት ነው። ሚካኤል የሚለው ስም ቃሉ የዕብራይስጥ ነው፤ ሚ - የሚለው «መኑ» ማለት ነው፥ ካ - የሚለው «ከመ» ማለት ሲሆን፥ ኤል - ማለት ደግሞ «አምላክ» ማለት ነው። ይህን ማለትም የቅዱስ ሚካኤልን ስም በጠራን ቊጥር የምንመሰክረው ስለ እግዚአብሔር ነው፤ በመሆኑም እግዚአብሔርን በባሕርይ የሚመስለው፥ በሥልጣንም የሚተካከለው፥ በምድርም በሰማይም እንደሌለ የሚናገር ልዩ፥ ክቡር ስም ነው። የነቢያት አለቃ ሙሴ ባሕረ ኤርትራን ለሁለት ከፍሎ ሕዝቡን ያሻገረለትንና ፈርዖንን ከነሠራዊቱ ያሰጠመለትን አምላክ እግዚአብሔርን በመዝሙር ሲያመሰግን፥ «አቤቱ በአማልክት መካከል (በስም አማልክት ከሚባሉ፥ በስመ አማልክት ከሚጠሩ፥ አንድም አማልክት ዘበጸጋ ከተባሉ ከነቢያት ከካህናት መካከል) አንተን የሚመስል ማነው? በቅዱሳንም ዘንድ እንደ አንተ የከበረ ማነው?» ብሏል። ዘጸ ፲፭፥፲፩። ቅዱስ ዳዊትም፦ «አቤቱ፥ ከአማልክት የሚመስልህ የለም፤» ብሏል። መዝ ፹፭፥፰። 
 ህዳር ወር በዐሥራ ሁለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ሲመት በታላቅ ድምቀት  ታከብረዋለች ፡፡ እንደ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምህሮ ዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በአሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው ፡፡እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል፡፡(ይህን ሁለተኛውን ሹመት ያገኘው በሚያዚያ 2  እንደሆነ አክሲማሮስ በሚባለው የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ አናገኛለን፡፡)

የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ ግን አይደለም ፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይም ጭምር ነው ፡፡ ይህም እንደሆነ እንድንረዳ በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባለውን እስራኤል ዘሥጋን ሲራዳና ሲጠብቅ እንደነበረ ተጽፎልን እናገኛለን ፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍ ቅዱስ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ በኢያሪኮ ምድረ በዳ እንደተገለጠለት “… ዐይኑን አንሥቶ ተመለከተ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ የያዘ ሰው በፊቱ ቆመ ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ ? አለው ፡፡ እርሱም “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቼአለሁ”(ኢያ.5፡13) ይለናል፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ነፃ ሲያወጣቸው ይመራቸው የነበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር ፡፡ ሹመቱ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይም በመሆኑ ስለ እነርሱ ዲያብሎስ ይዋጋው ፣ በጸሎትም ይራዳቸው ነበር ፡፡ ነገር ግን ኃጢአት ሠርተው ሲያገኛቸው ለእግዚአብሔር አድልቶ ኃጢአተኞችን ስለሚቀጣ እግዚአብሔር ሕዝቡን “በፊቱ ተጠንቀቁ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት”(ዘጸ.23፡21)ብሎ አስጠንቅቋቸው ነበር ፡፡ ይህም ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ መሾሙን ያስረዳናል ፡፡ ነገር ግን ከላይ የተጠቀሱት ጥቅሶች ሕዝበ እስራኤልን ይራዳቸው የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ስለመሆኑ አያረጋግጥም የሚል ካለ “መልአክ” የተባለው ቅዱስ ሚካኤል ስለመሆኑ ቅዱስ ገብርኤል ወደ ነቢዩ ዳንኤል በተላከ ጊዜ ገልጦልን እናገኛለን፡ሰይጣን ሠራዊቱን አሰማርቶ በአሕዛብ ነገሥታት እያደረ የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባሉ እስራኤልን ዘወትር በጦርነት ያስጨንቃቸው ነበር። በዚህም ምክንያት ሲወድቁ ሲነሡ፥ ሲነቀሉ ሲተከሉ፥ ሲፈርሱ ሲገነቡ፥ ሲበተኑ ሲሰበሰቡ፥ ሲሰበሩ ሲጠገኑ ኖረዋል። በዚያ ዘመን መጋቤ ብሉይ ተብሎ የሚታወቀው ቅዱስ ሚካኤል ነው። እርሱም ዘወትር ከቅዱስ ገብርኤል ጋር ሆኖ ሕዝቡን ይረዳቸው ነበር። ይኽንንም «ወደ አንተ የመጣሁት ለምን እንደሆነ ታውቃለህን? አሁንም የፋርስን አለቃ እዋጋው ዘንድ እመለሳለሁ፥ እኔም ስወጣ እነሆ የግሪኮች አለቃ ይመጣል። (ሰይጣን በግሪክ ንጉሥ አድሮ ሌላ ጦርነት ይጀምራል)። ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፥ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ (ከመላእክት አለቃ) ከሚካኤል በቀር የሚያጸናኝ የለም።» ዳን ፲፥፳፩ በማለት ቅዱስ ገብርኤል ለነቢዩ ለዳንኤል ነግሮታል። ቅዱስ ገብርኤል እንዲህ ካለ እኛስ ምን እንበል? 
የእግዚአብሔር ቸርነት፥ የድንግል ማርያም አማላጅነት፥ የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት አይለየን አሜን።
  



Friday, November 18, 2011

‹‹አእምሮሽ የተመሰገነ ይሁን!››



ዘወትር ከአባታችን ሆይ ቀጥሎ በምናደርሰው ‹‹በሰላመ ገብርኤል›› በተሰኘው የጸሎት ክፍል ውስጥ ‹‹በሐሳብሽ ድንግል ነሽ በሥጋሽም ድንግል ነሽ›› የሚል የምስጋናና የምስክርነት ቃል ይገኛል፡፡ በተመሳሳይ መንገድ በመልክዓ ማርያም ውስጥም ‹‹ሰላም ለሕሊናኪ ሐልዮ ሠናያት ልማዱ ወገቢረ ምሕረት መፍቅዱ›› ማለትም ‹‹ምሕረት ማድረግ ለሚወድ መልካም መልካሙን ማሰብ ልማዱ ለሆነ ሕሊናሽ ሰላም እላለሁ!›› የሚል የምስጋና ቃል አለ፡፡
የተአምረ ማርያም መቅድም ደግሞ የድንግል ማርያምን ሕሊና ከመላእክት ሕሊና ጋር ያስተያይና በልጦ ሲያገኘው በመደነቅ እንዲህ እያለ ያመሰግናል፡፡ ‹‹ሥጋዊ ነገር ከማሰብ መጠበቅ ከአዳም ልጆች ለማን ተሰጠው? ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ለመላእክት እንኳን አልተቻላቸውም፡፡ በቀደመው ወራት ያልተሰጣቸውን ሽተው በድለው ከሰማይ ወደ ምድር ወርደዋልና፡፡›› ከዚህም ጋር አያይዞ ‹‹የእመቤታችን ማርያም አሳብ እንደ አምላክ አሳብ ነው፡፡›› ይህም አሳብዋ ንጹሕና መልካም ብቻ መሆኑን ያስረዳናል፡:
እኛ ክርስቲያኖች ‹‹እግዚአብሔርን እንድንመስል›› ታዘናል፡፡ (1ጢሞ4.7-8፤ 1ቆሮ11.1) ይህም በመልክ አይደለም፡፡ በሥራና በአመለካከት እንጂ፡፡ እግዚአብሔርን በአመለካከት መምሰል የማይቻል ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔርን ምሰሉ አንባልም ነበር፡፡ በመልክ ስለመምሰል የሚናገር ቢሆን ኖሮ ደግሞ መልክን የሚፈጥረው ፈጣሪ ስለሆን ‹‹ምሰሉ›› አንባልም ነበር፡፡ የሚደንቅ ነው! እኛ ፈጣሪን በአሳብና በአመለካከት እንድንመስለው ታዘዝን፡፡ ድንግል ማርያም ግን መስላ ስለተገኘች ‹‹አሳብዋ እንደ አምላክ አሳብ ነው፡፡›› የሚል ምስክርነት ተሰጠላት፡፡
ቀደም ሲል ስለ ድንግል ማርያም ፍጹም የሕሊና ድንግልናና በጎነት ከአዋልድ መጻሕፍት ያስቀደምኩት ሆን ብዬ ነው፡፡ ይህንን ትምህርት መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት እንደሚደግፈው ማሳየት ያስፈልጋልና እነሆ!
ብዙ ሰዎች ስለ ድንግል ማርያም የሕሊና ንጽሕና ስንናገር በምን አውቃችው ነው? ለማለት ይዳዳቸዋል፡፡ በእርግጥ እኛ እንኳን የድንግል ማርያምን ሕሊና የኃጥአንንም ሕሊና የምናውቅበት ችሎታ የለንም፡፡ የጻድቃን ሕሊና ከኃጥአን ይልቅ እጅግ ይጠልቃል፡፡ የድንግል ማርያም ሕሊና ደግሞ ከሁሉ ይልቅ ጥልቅ ነው፡፡ ‹‹መንፈሳዊ ሰው በማንም አይመረመርም እርሱ ግን ሁሉን ይመረምራል›› ከተባለ ሰው ፍጹም መንፈሳዊት ድንግል ማርያምን ሊመረምር እንዴት ይችላል? (1ቆሮ2.15)
ታዲያ ‹‹በሐሳብሽ ድንግል ነሽ›› እያላችሁ ጠዋትና ማታ የምትዘምሩት የእርሷን ሐሳብ በምን አውቃችው? ለሚሉን መልሳችን፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ድንግል ማርያም አሳብ ስለሚናገር ነው እንላቸዋለን፡፡ የት ቦታ ቢሉንም ቅዱስ ሉቃስ ሲጽፍ ‹‹ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው ብላ አሰበች›› ይላል፡፡ (ሉቃ1.29) ‹‹አሰበች›› ማለቱን ልብ በሉ፡፡ ይህን አለች ቢል ሰምቶ ነው፤ ይህን ሠራች ቢል አይቶ ነው ይባላል፡፡ ‹‹አሰበች›› ሲል ምን እንላለን? የክርስቲያኖች መልስ አንድ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ምን እንዳሰበች ገልጾለት ነው እንላለን፡፡ ሰይጣንና መናፍቃን የሚሉት አያጡምና ምናልባት ገምቶ ነው ሊሉ ይችላሉ፡፡ መቼም በዚህ አይሳቅም!!! መጸለይ ነው እንጂ፡፡
ይህ ብቻ አይደለም! በየርእሰ ጉዳዩ የድንግል ማርያም አሳብ ምን እንደሚመስል መንፈስ ቅዱስ ሲገልጥ ኖሮአል፡፡ ከዚህ የተነሣ ወንጌላዊው ሉቃስ አንድ ጊዜ ብቻ ሳይሆን ደጋግሞ ‹‹ይህን ሁሉ ነገር በልቧ እያሰበች ትጠብቀው ነበር፡፡›› ሲል መስክሯል፡፡ (ሉቃ2.19፤ ሉቃ2.51) መንፈስ ቅዱስ በልቧ ያለውን ካልገለጠለት ‹‹በልቧ እያሰበች ትጠብቀው ነበር›› እያለ ሊናገር እንዴት ደፈረ? በሰው ልብ ያለውን ከመንፈስ ቅዱስና ከሰውዬው በቀር ማንም ሊያውቅ እንደማይችል ቅዱስ ጳውሎስ ጽፎ የለምን? (1ቆሮ2.11)
ድንግል ማርያም በሕሊናዋ የዚህ ዓለም ምኞት አልነበራትም፡፡ እንኳን ኃጢአቱና ኃጢአት ያልሆነውም ሥጋዊ አኗኗር በልቧ አልነበረም፡፡ ይህም ማለት ‹‹አግብቼ ወልጄ መልካም እየሠራሁ ቤተሰቦቼን እየረዳሁ እኖራለሁ›› የሚለው አሳብና ምኞት በውስጧ አልነበረም፡፡ ይህም ፈጣራ ሳይሆን በቅዱስ ዳዊት የትንቢት ቃል ይታወቃል፡፡ ስለ እርሷ ‹‹ልጄ ሆይ ስሚ ጆሮሽን አዘንብዪ የእናትሽንና የአባትሽን ቤት እርሺ›› ብሏል፡፡ ምእመናን! አባቷ ዳዊት እረ ስሚኝ፣ ጆሮ ስጪኝ እያለ ለምኖ ሲያመሰግናት ስሙ!!
‹‹እርሺ›› ማለት ምን ማለት ነው? አታስቢ ማለት አይደለምን? የምትረሳውስ ምንድር ነው? የእናት የአባቷን ቤት ነው፡፡ ይህ ማለት የእናት የአባትሽን ቤት አትመኚ! እንደ እነርሱ አግብቼ፣ ወልጄ እኖራለሁ ብለሽ አታስቢ ማለት ነው፡፡ ልብ በሉ! ቅዱስ ዳዊት ነቢይ ነው፡፡ እርሷ ይህን ዓለም እንድትረሳ የመከራት እንዳይመስላችሁ፡፡ እንደምትረሳው አውቆ በፈሊጥ ትንቢት ተናገረ እንጂ፡፡ አነጋገሩ እኮ ‹‹አቤቱ ተነሥ›› እንደሚለው ዓይነት ትንቢት ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊት ይህን ቃል ብዙ ጊዜ ደጋግሞ ስለኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ተናግሮታል፡፡ (መዝ131.8) ኢየሱስ ክርስቶስ ዳዊት ‹‹ተነሥ›› ስላለው የተነሣ ይመስላችኋል? እንደሚነሣ አውቆ ትንቢት መናገሩ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ እንዲሁ ‹‹እርሺ›› ቢልም እንደምትረሳው አውቆ ትንቢት ተናገረ እንጂ ያስረሳት ዳዊት አይደለም፡፡
ታዲያ እንዲህ ኃጢአትን ሁሉ የዘነጋ ሕሊና ለማን ተሰጠው? እንዲህ ያለ ንጽሕናንና ቅድስናን የማያመሰግን አንደበት እንደምን ያለ ነው? እንዴት ያለ በደል ነው? እንዴትስ ያለ ድፍረት ነው? በበደል የረከስን ስንሆን ኃጢአትም ነግሣብን ሳለ ራስን ከፍ ለማድረግ ላላፈርን ለኛ ወዮታ ይገባል! እንኳን ከኀልዮ ኃጢአት ከተግባሩም ላልሸሸን ለኛ ኀዘን ይገባል፡፡ ‹‹እርሷ እንደኛው ናት!›› የሚሉ አርሲሳን /መናፍቃን/ ቦታቸው የት ይሆን? ሰው ባለማወቁ መጥፋቱን አያውቅም፡፡ መሬታዊው ሰው ደረጃውን አላዋቀምና ለዚህ ስንፍናው ከእግዚአብሔር ዘንድ ምላሹ ምን ይሆን?
ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስ! ድንግል ማርያም መልአኩን ‹‹ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል›› አለችው፡፡ መልአኩ ‹‹እነሆ ትጸንሻለሽ›› ባላት ጊዜ ታዲያ ምን ብርቅ አለው? ‹‹ሴት ልጅ ጊዜዋ ሲደርስ ታገባለች፤ ትጸንሳለች›› ልትለው ትችል ነበር፡፡ እርሷ ግን ‹‹ይህ እንዴት ይሆናል?›› አለችው፡፡ ይህም ጥያቄዋ የልቧን መታተም ያስረዳል፡፡ አንዲት ሴት ባል ባይታጭላትና ባታገባ እንኳን ትወልጃለሽ ስትባል ‹‹ይሆን ይሆናል›› ትላለች፡፡ ወንድ ግን በተፈጥሮው የሚወልደው እርሱ ስላልሆነ ትወልዳለህ ቢሉት ‹‹እንዴት ይሆናል?›› ይላል፡፡ የድንግል ማርያም ንግግር የሁለተኛውን ይመስላል፡፡ የወንድ መውለድ የማይጠበቅ ነገር እንደሆነ በእርሷ ዘንድ መውለድ የማታስበው ጉዳይ ነውና ‹‹እንዴት ይሆናል›› አለች፡፡
እንደዚሁም መልአኩን ‹‹ወንድ ስለማላውቅ›› ብላዋለች፡፡ ይህም ለወደፊት እንኳን ወንድ ላለማወቅ ሕሊናዋን የዘጋች መሆኗን ያስረዳል፡፡ አለማወቋም ጾታ የመለየትና ያለመለየት ጉዳይ አይደለም በግብር ነው እንጂ፡፡ ለዮሴፍ የታጨችው ለተቃርቦ ቢሆን ኖሮ ወንድ ስለማላውቅ ባለችው ጊዜ መልአኩም መልሶ ምነው ዮሴፍ አለ አይደል ሊላት በቻለ ነበር፡፡ ነገር ግን መልአኩ እንደዘመናችን መናፍቃን አያስብምና የልቧን ንጽሕና አይቶ በግብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክን እንደምትወልድ ነገራት፡፡ ለማሳመንም ‹‹ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም›› አላት እርሷም ነገሩን በጥንቃቄ መርምራ ስታበቃ ‹‹ይደረግልኝ›› ብላ በትሕትና ቃሉን ተቀበለችው፡፡ ያን ጊዜ አካላዊ ቃል ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋ ነፍስ ነሥቶ የዕለት ጽንስ ሆኖ በማኅፀኗ አደረ፡፡


የሕሊናዋ ነገር እንደዚህ ከሆነ ቅዱስ ዳዊት ‹‹አእምሮሽ የተመሰገነ ይሁን!›› በማለት ሰው እንዳይገድል እጁን ከደም የከለከለችውን ሴት አእምሮ ካመሰገነ እኛ ክርስቲያኖች ድንግል ማርያም በቀን ስንት ጊዜ ‹‹በሐሳብሽ ድንግል ነሽ›› እያልን ልናመሰግናት ይገባን ይሆን? (1ሳሙ25.33)

by
ዲያቆን ኅብረት የሺጥላ

Thursday, November 17, 2011

በአቡነ ፋኑኤል ሥርዓት አልበኝነት የተቃውሞ ሕዝባዊ ጥሪ ለመላው ዓለም



ለዋሺንግተን ዲሲ እና አካባቢው ነዋሪዎች በሙሉ!

አቡነ ፋኑኤል በገጠማቸው ቀውስ እንዳዘኑ!
 ከትላንት በስቲያ ሰኞ ከቀትር በፊት አቡነ ፋኑኤል በድብቅ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ገብተው ማደራቸው ተዘግቧል፥ በእለት በገቡበት ዕለት ከፍተኛ ተቃውሞ እንደሚገጥማቸው ተገምቶ ስለነበር ቀድመው ለሰዎች ሐሙስ ብለው በሀሰት ፕሮፓጋንዳ አስነግረው ነገር ግን እሳቸው ሰኞ ከእኩለ ቀን በፊት ማንም ሳይሰማ ወደ ከተማው ገብተው አድረዋል። በዚሁ እለት በቨርጂኒያው አየር ማረፊያ እንደደረሱ አጠገባቸው ሆነው እርሳቸውን እና አላማቸውን በመደገፍ የሚታወቁት የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካሕናት እንዲሁም ከአካባቢው ካሕናት እነ ቀሲስ ታደሰ ሲሳይ እና በቀሲስ ኢስሃቅ አማካኝነት ከአየር ማረፊያ ተቀብለዋቸው በቀጥታ በደቡብ ምዕራብ ዋሽንግተን  ወደሚገኘው የደብረ ምሕረት ገንዘብ ያዥ ወደ ሆነው ሰው መኖሪያው ቤት በቀጥታ አምርተው በዛው ቀናትን ለማሳለፍ ተገድደዋል። ባለፈው እንደዘገብነው በዚህ ጉዞዋቸው በጋሻውን ይዘው ለመምጣት ብዙ ጥረቶችን ለማድረግ ቢሞክሩም የተሳካላቸው አይመስልም፣ ነገር ግን እርሱን ለማምጣት የሚቻላቸውን እንደሚያደርጉም ቅዱስ ፓትሪያሪኩም ቃል እንደገቡላቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ።
አንድ የአካባቢው ክርስቲያን በዛሬው ዕለት በላከልን መልዕክት እንደሚያስረዳን በመጪው እሁድ የሚከበረውን የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ለማክበር የመጡት አቡነ ፋኑኤል ከባድ ተቃውሞ እንደሚገጥማቸው ከወዲሁ በመረዳት የደብሩ የቦርዱ አባላት አስቸኳይ ስብሰባ አድርገው የሚከተሉትን መመሪያዎች አስተላልፈዋል

፩ኛ/ በክብረ በዓሉ ቀን ማንም ሰው መኪናውን በጊቢው ውስጥ እንዳያቆም (ለጸጥታ ስለማይመች)
፪ኛ/ ከአካባቢው የፓሊስ ቢሮ ከሁለት እስከ አራት የፓሊስ ሰራዊት በቦታው ተገኝቶ ክብረ በዓሉን እንዳይታወክ እንዲቆጣጠሩ
፫ኛ/ አቡኑም ምንም አይነት ንግግር እንዳያደርጉ
፬ኛ/ ቢቻል በዑደቱም ላይ ባይኖሩ የሚሉትን መመሪያዎች አስተላልፏል።

ከዚህ የቦርዱ መመሪያ እንደምንረዳው በደብረ ምሕረት አካባቢ አቡኑ ከመጡ ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ አለመረጋጋት እና መሸበር እንዳለ ከአካባቢው መረጃውን ያደረሱን ክፍሎች ያስረዳሉ። በተያያዘ ዜና በዚሁ እሑድ በሚደረገው የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ላይ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ተቃውሞ እንደሚደረግ ከዚህ ጋር አያይዘው ገልጸውልናል፣ በመጪው እሑድ ከፍተኛ ትዕይንቱን በማዘጋጀት ላይ ያሉት ወገኖቻችን እንዳስረዱን ከሆነ አላማቸውን በግልጽ አስቀምጠው የአቡነ ፋኑኤልን አስተዳደርም ሆነ ውክልና አንቀበልም። ልክ እንደ ከዚህ በፊቱ በተለያዩ የሀገራችን የኢትዮጵያ ክፍሎች ተመድበው ሥራ ከመስራት ይልቅ መከፋፈልንን እና ሕዝብን በሕዝብ ላይ በማነሳሳት ሥራ ላይ ተሰማርተው አብሮ ለብዙ ዘመን የኖረውን ሕብረተሰብ ለያይተው ሲያበቁ እርሳቸውም ከሀገረ ስብከታቸው በሕዝቡ ብሶት እና በቅዱስ ገብረኤል ረዳትነት ከቦታቸው ተነስተዋል። እዛ በነበሩባቸው ጊዚያት አቡነ ፋኑኤል "እኔ አሜሪካው ነኝ ምንም ልታደርጉኝ አትችሉም" እያሉ በደሃው ሕዝብ ላይ ሲንቀባረሩ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፣ ሆኖም በአሁን ሰዓት ቤተ ክርስቲያንንም ወክለው ይሁን በገንዘብ ገዝተውት ወደ ዋሺንግተን አመጣታቸውንም ሆነ ውክልናቸውን እንደማይቀሉ አስታውቀው፣ ጥያቄያቸውንም በአቸኳይ የማይመልሱ ከሆነ ማንኛውንም እርምጃ ለማድረስ ማንኛውንም ዝግጅት አድርገው ለዚህም ደግሞ በማንኛውም መልኩ የገንዘብም ሆነ የሰው ሃይል በሚገባ ስላላቸው በሕግም ይሁን ከሕግ ውጪ አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጅታቸውን እና ቁርጠኝነታቸውን አሳውቀውናል።

በቤተ ክርስቲያኑ አካባቢም ምዕመናኑ፣ አገልጋዮች ካሕናት እንዲሁም ዲያቆናት ለሁለት እነደተከፈሉ ይነገራል። በአገልጋይ ሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በኩል ባለፈው እሑድ ተሰባስበው ግማሹ የሰንበት ት/ቤት ከአየር ማረፊያ ሄደን መቀበል እና ማጀብ ይኖርብናል ሲሉ እንዲሁ ግማሹ ደግሞ አይደለም አየር ማረፊያ ሄደን ልንቀበላቸው እዚህ መቀመጥ የለባቸውም፣ እስከ ዛሬ ድረስ በእንግድነት ነው ተቀብለናቸው ያስተናገድናቸው ከዚህ በኃላ ግን ሥልጣኑን በምንም መንገድ ያግኙት እኛ ከዚህ በኃላ ሊወክሉንም እንደ አባት ልንቀበላቸውም አንችልም በማለት አማረው ተናግረዋል። በአገልካይ ካሕናትም በኩል ገሚሶቹ ምን ችግር አለው ተቀብለን ማገልገል ነው እንደውም እስከ ዛሬ ድረስም የሳቸውን ሥም ነው ጠርተን ሥርዓተ ቅዳሴውንም የምንፈጽመው አሁን ደግሞ ሕጋዊ ወኪል ስለሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ስለላካቸው መቀበል የግዴታችን ነው በማለት በብልጥነት ለማስቀመጥ ይሞክራሉ። ከፊሎቹ ደግሞ የሰንበት ት/ቤቱ ዓይነት ተመሳሳይ አቋም ይዘው እስካሁን ስማቸውን የምንጠራው ከሰሩት ሥራ አንፃር ነው እንዲሁም ባለቤትነቱ የርሳቸው ስለሆነ ነው ይሁንና ከዚህ በኃላ እርሳቸውን እንደ ዋሽንግተን ዲሲ እና የምዕራብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብንቀበል ፓትሪያሪኩን የመቀበል እና በሥርዓተ ጸሎቱ ላይ የመጥራት ግዴታ ሊመጣብን ይችላል፥ ያማለት ደግሞ ሕዝባችንን በጣም ስለሚያስቆጣው ይሄኛው አካሄድ ሊያዋጣን አይችልም በሚል ከፍተኛ ተቋውሟቸውን ግልጸዋል። እንደ መረጃ አቀባያችን አገላለጽ ከሆነ በማንኛውም መልኩ የደብረ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ከዚህ በኃላ ለሁለት ወይም ለሦስት ቦታ የሚከፋፍለው መንገድ እንዳለ በግልጽ አሳይቷል በመሆኑም የአቡነ ፋኑኤል አመጣጣ በማንኛውም መመዘኛ የአካባቢውን ሕዝብ ቀርቶ የደብረ ምሕረትን ሕዝበ ክርስቲያን እንኳ ሊወክሉ እንደማይችሉ ከወዲሁ ተፈርቷል፣ አንዳንድ የቤተ ክርስቲያኗ ሕልውና ያሰጋቸው ምዕመናንም የፊርማ ማሰባሰቢያ እና ደብዳቤ አዘጋጅተው ለወከላቸው ለቅዱስ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲነሱልን ሲሉ ደብዳቤዎችን እና የፊርማ ማሰባሰቡን ሥራ ከወዲሁ እንደጀመሩት ከወዲሁ ለማወቅ ተችሏል።

ከዚህ በተጨማሪ በዚሁ በመጨው እሑድ ህዳር ፲ ቀን (Nov. 20, 2011) ማለትም የቅዱስ ሚካኤል በዓለ ንግስ እለት ታላቅ የሆነ ሕዝባዊ ተቃውሞ እንደሚያደርጉ እና አስፈላጊውን ሁሉ ቅድመ ዝግጅት አድርገው እንደጨረሱ እና የእያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ እርዳታ እና ትብብር በመጠየቅ አስፈላጊውን ትብብር እንዲደረግላቸው ከወዲሁ ጥሪ እንድናደርግላቸው ከመልዕክቱ ጋር ተያይዞ ደርሶናል። በዚህ ሕዝባዊ ተቃውሞ ላይ እያንዳንዱ ሀገር ወዳድ እና የኦርቶዶክሳዊ ቤተ ክርስቲያኑ ሥርዓት ግድ የሚለው ሁሉ የዚህ ሕዝባዊ ተቃውሞ ተካፋይ እንዲሆን ከወደሁ አዘጋጆቹ አስቀድመው ጥሪያቸውን አድርሰውልናል። የዚህ ዝግጅት አስተባባሪዎች እንደገለጹልን ከሆነ አቡነ ፋኑኤል እና ተባባሪዎቻቸው ይሄንን ክብረ በዓል ተጠቅመው የቪዲዮ ቀራጭ ባለሙያ ግምቱ $2000.00 ብር ከፍለው በቪዲዮ አስቀርጸው እና አቀናብረው ልክ ሕዝቡ እንደተቀበላቸው አስመስለው "ሕዝቡ ተቀብሎናል ሃሳብ አይግባችሁ" ብለው ፕሮፓጋንዳቸውን ለመሥራት እና ወደ ኢትዮጵያም ለመላክ ቅድመ ዝግጅትም እያደረጉ እንደሆነ ከወዲሁ ለመረዳት ተችሏል። አባ ፋኑኤል እና ግብረ አበሮቻቸው እንዲህ ዓይነት ትውልድን የማያንጽ ሥራ እየሰሩ፣ ጽድቅ ያይደለ ተንኮል፣ እውነት ያይደለ ሐሰት የተሞላበት እየሰሩ እንደገና ልክ በጣም ትጉህ የሆኑ ዓይነት መለስ ቀለስ በማለት ሰውን ለማወዳበድ የሚያደርጉትን ሤራ እና ተንኮል ከወዲሁ ልንገነዘብ ያስፈልጋል እንላለን። አሁንም ሥራ ሰርተናል ብለው ለማለት እንዲህ አይነት ድራማ በማን ላይ የሠሩ እንደሆነ ያልተገነዘቡት እነዚህ ክፍሎች ከተንኮል ይልቅ፣ ትህትና፣ ከበደል ይልቅ ፍቅርን ቢማሩ እና ቢያስተምሩ ይሻላል እንላለን። እነዚህን ሁሉ የተንኮል እና የድራማ ዝግጅቶችን ለመሥራት መዘጋጀታቸው በራሱ እራሳቸውን እና ሕሊናቸውን እያታለሉ ጊዜያቸውን ለመፍጀት ያሰቡ አባት እንጂ ለሥራ የመጡ አባት እንዳልሆኑ ይሄ ሥራቸው እራሱ ትልቅ ምስክር ነው በማለት አዘጋጆቹ በምሬት ገልጸውልናል።

ቸር ወሬ ያሰማን፣ አጽራረ ቤተ ክርስቲያንን ያስታግስልን አሜን
የመላው ዓለም የተዋሕዶ ቤተሰብ

ጥቅምት 11 ቀን 2004 ዓ.ም. የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የተቃውሞ ሰልፍ እይታዎች

 ቪሲዲውን ለመመልከት እዚህ ይጫኑ
ጥቅምት 11 ቀን 2004 ዓ.ም. የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በአዲስ አበባ መንበረ ፓትርያሪክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተሐድሶ መናፍቃን ላይ ያደረጉትን የተቃውሞ ሰልፍ የሚያሳይ የ 20 ደቂቃ ቪሲዲ ለዛሬ አቅርበንላችኋል
በሰልፉ ላይ በአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት ከሚገኙ የ131 ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ያላቸውን የደንብ ልብስ(ዩኒፎርም)እና ነጠላ በመልበስ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምቱ ጉባዔው በተሐድሶ መናፍቃን ላይ እርምጃ እንዲወስድ ሲያሳስቡ ይታያል፡፡ ወጣት የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎቹ ተቃውሞአቸውን በአደባባይ ከማሰማታቸው በፊት ቀደም ባሉት ጊዜያት መዋቅራቸውን ጠብቀው ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤትና ጉዳዩ በቀጥታ ለሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን አካላት የተሐድሶ መናፍቃንን ማንነት የሚያጋልጥ ባለ 261 ገጽ የጽሑፍ ሰነድና 14 የምስል እና የድምጽ(VCD) ሰነድ በማስረጃነት ማቅረባቸው ቢታወቅም አደባባይ ለመውጣት እነዳላሰቡ ሆኖም ግን እነ በጋሻው፣ትዝታው፣አሰግድ፣ናትናኤል፣ያሬድና ሌሎችም የተሐድሶ ሎሌዎች ስማችን ጠፋ፣ መድረክ ተከለከልን፣ ተሐድሶ የሚባል የለም ፣ወዘተ….በማለት በለመዱት የግራ ዐይን የአዞ እንባቸው ሕዝቡን ለማሳሳት ሰልፍ እንወጣለን ብለው በማወጃቸው ምክንያት ወጥተው ተቃውሞአቸውን እንዳሰሙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ቪሲዲው፦
• “የዘማሪ” ትዝታው ሳሙኤልን መደብደብና መዋከብ ኋላም በድንጋጤ ጥግ ላይ ተደብቆ ጥርሱን እየነከሰ መንቀጥቀጥን፣
• የተሐድሶ መናፍቅ አሰግድ ሳህሉን ተንኮሳና መንቀዥቀዥ ኋላም መደንገጥና መሸማቀቅን፣
• የ“ዘማሪት” ቅድስት ምትኩንና “ዘማሪት” የትምወርቅን ድፍረትን፣
• የመናፍቁ ናትናኤል ታምራት በፍርሃት ታጥሮና ጥግ ይዞ መታየትን፣
• የ“መምህር” ተረፈን የመሃይም ድፍረትና በኋላም ቅሌትና ውርደት፣
• የሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴንና የቅ/ማርያም ገዳም አስተዳዳሪ አላዋቂነትና አድርባይነትን፣
• የአዲስ አበባን ሰንበት ት/ቤቶች በወኔ የታጀበ ጠንካራና የተደራጀ ተቃውሞን፣
• የቅዱስ ፓትርያርኩን ብስጭትና ወገንተኛነት፣
• የአዲስ አበባና የፌዴራል ፖሊሶችን የተረጋጋ፣ሕጋዊና ሰላማዊ የጸጥታ ማስተባበር ሥራን፣
• የአዲስ አበባ ምዕመናንን እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን ቅናት ወዘተ…..በአንጻሩ ደግሞ የተሐድሶ መናፍቃንን ድፍረትና አይን አውጣነት ያሳያል፡፡
• የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ቤተ ክርስቲያናችን በተሐድሶ መናፍቃን አትወረርም የሚል አገር አቀፍ ብሎም ዓለም አቀፍ የሆነ አጀንዳ ይዘው ታይተዋል፤
ቪሲዲው ከ“ዘማሪያኑ” እነ ትዝታው ሳሙኤል፣የትምወርቅ፣ቅድስት ምትኩ፣ምርትነሽ ጥላሁን፣ሃብታሙ ሽብሩ፣ሐዋዝ ተገኝ፣…..ከ“መምህራን” ናትናኤል ታምራት፣አሰግድ ሣህሉ፣ተረፈ፣ጋሻዬ መላኩ፣ስንታየሁ፣በፈቃዱ፣ታሪኩ አበራ….ነበሩበት፡፡የአዲስ አበባ ምዕመናን “ፍንዳታ”እያሉ የሚጠሯቸው የመነኩሴ ቆብ ያጠለቁ የተሐድሶ መነኮሳትም ነበሩበት፡፡
እነበጋሻውና ያሬድ አደመ ከመጋረጃው ጀርባ ሆነው ማስተባበርን መርጠዋል፡፡ማንነታቸው እንዳይታወቅ ፊታቸውን በሰፊ መነጽር ለመሸፈን የሞካክሩ ኮረዳዎችም በሰልፉ ነበሩበት
ባአጠቃለይ ቪሲዲው አንድ ሰዓት ያህል ቢፈጅም እኛ ግን አሳጥረን በ20 ደቂቃ አቅርበንላችኋል። ሙሉውን ቪሲዲ በዚሁ  በደቂቀ ናቡቴ ጦማረ መድረክ በቅርቡ የምንለቀው ይሆናል። ቪሲዲው ኤዲት ስለሚጎድለውና ስለ ድምፁ ጥራት ይቅርታ እንጠይቃለን። 
እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያናችንን ይጠብቅ አሜን።

Friday, November 4, 2011

የቅ/ሲኖዶስ ጉባኤ 12ኛ ቀን ስብሰባ ዋና ዋና ዜናዎች



 (ደጀ ሰላም፤ ጥቅምት 24/2004 ዓ.ም፤ ኖቬምበር 4/2011)፦
  • አቡነ ፋኑኤል ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን በሽምግልና በመጠቀም በዋሽንግተን ዲሲ እና በካሊፎርኒያ የሚጠብቃቸውን መሬት አንቀጥቅጥ ተቃውሞ ለማብረድ እና የአሜሪካ ሹመታቸውን ለማደላደል እየተጣጣሩ ነው፤
  • ቅ/ሲኖዶስ በመ/ፓ/ጠ/ጽ/ቤት አስተዳደራዊ እና መዋቅራዊ ችግሮች ላይ የቀረበው የዳሰሳ ምልከታ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በሚመራ የባለሞያዎች ኮሚቴ እንዲገመገም ወሰነ፤
v  በኤፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 34 ንዑስ አንቀጽ 5 መሠረት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክን የፌዴራል መንፈሳዊ ፍርድ ቤቶችን እንደገና ለማቋቋም፣ ለማደራጀት እና ለማጠናከር የተዘጋጀውን ዐዋጅ ረቂቅ መርምሮ በማስተካከል በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሕግ ዕውቅና እንዲያገኝ ይላክ ዘንድ መርቷል፤ መንፈሳዊ ፍ/ቤቶቹ የመንግሥትን የፍትሕ አካላት ላጨናነቁት የቤተ ክህነት ጉዳዮች እፎይታ እንደሚሰጡ ተስፋ ተደርጓል፤
v  የጋብቻ፣ ፍቺ፣ ቀለብ አወሳሰን፣ አካለ መጠን ያልደረሱ ሕፃናት ሞግዚትነትና በቤተሰብ ተዛምዶ ላይ የሚነሡ ጥያቄዎች፣ የውርስ፣ የኑዛዜና የስጦታ ጉዳዮች፣ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ከሚሰጡት መንፈሳዊ አገልግሎት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣ ከላይ በተገለጹት ጉዳዮች ላይ በሚቀርቡ ክሶች ኪሳራ መወሰን የፍ/ቤቶቹ የወል ዳኝነት ሥልጣን ክልል የሚሸፈኑ ናቸው፡፡
v  በፍ/ቤቶች ጉዳያቸው የሚታየው በቤተ ክርስቲያን የሃይማኖት ሥርዐት በፍ/ቤቶቹ ለመዳኘት ተስማምተው በፈቃዳቸው የቀረቡ አገልጋዮች እና ምእመናን ናቸው፡፡
v  ፍ/ቤቶቹ በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ የሚቋቋሙ ሲሆን መሪዎቹ ‹‹ርእሰ ፍትሕ›› የሚል ማዕርግ ይሰጣቸዋል፤
  • ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ በአጀንዳ ውኃ ቅዳ ውኃ መልስ ተጠምደዋል - አቡነ ሳሙኤልን ስለ ወነጀሉበት ክስ፣ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ስለ ማሻሻል እና ስለ ተጨማሪ ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ጉዳይ ቀደም ሲል በምልአተ ጉባኤው ውድቅ የተደረጉባቸውን ጉዳዮች በተለያየ ቀለም መልሰው ቢያነሡም ዳግመኛ ተቀባይነት ሳያገኙ ቀርተዋል፤
  • አባ ሰረቀ ‹‹ከሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ ዋና ሐላፊነታቸው እንዲነሡ በቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የተላለፈውን ውሳኔ ለመቃወም›› በሚል የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ሠልጣኞች በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት መካከል የተቃውሞ ፊርማ እያሰባሰቡ ነው፤ የደቀ መዛሙርቱን የጋራ ጥያቄዎች ለሽፋንነት ይጠቀማሉ የተባሉት ተቃዋሚዎቹ በአባ ሰረቀ ላይ በተላለፈው ውሳኔ ሁነኛ ሚና ተጫውተዋል ባሏቸው ማረፊያ ቤታቸው በቅጽሩ በሚገኘው ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል እና ሌሎች በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ላይም እንዳነጣጠሩ ተጠቁሟል፤ እንቅስቃሴውን አባ ሱራፌል የተባሉት የፓትርያርኩ ዘመድ እና ከአራት ያላነሱ “የፕሮቴስታንታዊ-ተሐድሶ-ኑፋቄ ጭፍሮች ናቸው” የሚባሉ (ዲ.ን አብርሃም ይገዙ - ከነገሌ ቦረና፣ ዲ.ን በረከት ታደሰ - ከአሰበ ተፈሪ፣ ዲ.ን መስፍን ታዬ - ከሐዋሳ፣ ዲ.ን አሳምነው ዐብዩ - ከአምቦ የመጡ እና በልደታ አካባቢ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መደበኛ ሥልጠና የወሰዱ) እና ዲ.ን መንግሥቱ - ከባሕር ዳር የተመደበ ያስተባብሩታል፤ ፓትርያርኩ አጋጣሚውን በመጠቀም የአባ ሰረቀን ጉዳይ መልሰው ሊያነሡ እንደሚችሉ ተገምቷል፤
  • በ17ኛ ተራ ቁጥር በተመለከተው ልዩ ልዩ አጀንዳ ሥር ፓትርያርኩ ለውይይት ያቀረቡትና “ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ላይ ከሐዋሳ መጥተዋል በተባሉ ሰዎች ቀርቧል የተባለውን ክስ” ቅ/ሲኖዶሱ ውድቅ አድርጎታል፣      
  • በተመሳሳይ “በልዩ ልዩ” ሥር ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ደብረ ሊባኖስ ገዳም፣ አክሱም ጽዮን ማርያም፣ ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም እና ቅዱስ ላሊበላ ደብር በጳጳሳት እንዲመሩ ያቀረቡት ሐሳብ በምልአተ ጉባኤው አባላት ተቀባይነት አላገኘም፤ በዚሁ አጀንዳ ሥር የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ደርበው የሚመሩት ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቀውስጦስ የመልቀቂያ ጥያቄ ያቀርባሉ ተብሏል፤
  • ከወትሮው በተለየ ለተከታታይ 13ኛ ቀን ቀጥሎ የሚገኘው የጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ቃለ ጉባኤዎቹንና የስብሰባውን መግለጫ ረቂቅ  በመናበብ ይፈራረማል፤ የምልአተ ጉባኤው ውሳኔዎች ተፈጻሚነት ጉዳይ አሳሳቢ እየሆነ ነው።

ቸር ወሬ ያሰማን፣
አሜን