Friday, September 21, 2012

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተግዳሮቶቿስ ምንድናቸው??? በክርስቶስ ደም የተመሠረተች ቤተክርስቲያን ልዕልናዋ ተጠብቆ ይቀጥል ዘንድ ምን ይጠበቃል ??

  • የስድስተኛው ፓትርያርክ ምርጫና መሰል ጉዳዮች በጥቅምቱ ቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ይወሰናል::
  • ቅዱስ ሲኖዶስ ከፓትርያርክ ምረጫ ጋር በተያያዘ ለቤተ ክርስቲያኗ ወሳኝ ጉዳዮችን እንደሚያስተላልፍ ይጠበቃል፡፡
(ደቂቀ ናቡቴ መስከረም 12/2005) ኢትዮጵያ ታላላቅ ቅዱሳንን ያፈራችበትን ወርቃማ ዘመንን ለመድገም ከአሁን የተሻለ ታላቅ አጋጣሚ ይመጣል ተብሎ መቼም የሚጠብቅ አይሆንም፡፡ ፈር ያጡት ሰርዓቶቻችን መስመር የሚይዙበት ፣ ምንም ስርዓት ያልተሰራላቸው ጉዳዮች አዲስ ስርዓት ተዘርግቶላቸው የወደፊት መጭውን እድል የምትወስንበት ፣ እንደ ግመል ያበጡትን ከፍተኛ ችግሮቻችንን የሚወገዱበት ፣ የምንፈታበት ጊዜ ከዚህ የተለየ አጋጣሚ ምቹ ሊመጣ? የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ወርቃማዎቹ ጊዜያት ዛሬ ላለነው ትውልድ ሲናፈቁን የሚኖሩ ቢሆንም እንዲህ ያሉ ትውልድን የምንፈጥረው እጅ ለእጅ ተያይዘን ተከባብረን በአንዲት ቤተክርስቲያን ያለሰለሰ ጥረት ስናደርግ ፣  ስርዓቶቿን ስናስጠብቅና ስንጠብቅ ፣ ማንም እንዳሻው ሲፈነጭ አይቶ ዝም እየተባለ የሚታይበትን ጊዜ ሲከስም መሆነ ግልጽ ነው፡፡  
በዚህ አጋጣሚ ይህ ጊዜ ካለፈን እና መሠረታዊ ችግሮቻችንን ሳናስተካክል የነበረው ስርዓት አለብኝነት ይቀጥል ብለን ዝም ካልን ግን ምን አልባትም ለቤተክርክስቲያናችን ጥቁር አሻራ አስቀምጠን እንዳልፍ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል፡፡ በተለይ ደግሞ የዘረኝነትና የፍቅረ ነዋይ ችግሮች መጥራት ካልቻሉ አደጋው የከፋ ይሆናል፡፡
የውስጥ ችግሮቻችን ምንም ብዙ ቢሆኑም ትኩረት ወስድን እያንዳንዱ ስርዓት እንዲስተካከል ካደረግን በአንድ ሀሳብና በአንድ ልብ ሆነን ከውጪ ጠላቶቻችን የሚመጣብንን የሰማዕትነት ጊዜያት እየናፈቅን ብሩህ ዘመንን እያየን በቃለ እግዚአብሔር የታነጸ ታላቅ ዜጋ ፣ ትውልድ የምንፈጥርበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡: በዚህ ረገድም የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን አርአያነት ለእኛም ይህ ተስፋ ይሆናል፡፡

በክርስቶስ ደም የተመሠረተች ቤተክርስቲያን ልዕልናዋ ተጠብቆ እንዲቀጥል ከምዕመናን ምን ይጠበቃል ?? ተግዳሮቶቿስ ምንድናቸው???

(ደቂቀ ናቡቴ መስከረም 11/2005) የምህላው ጊዜ ተፈፅመዋል ዛሬ ላይ በአንድ ልብ ሆነን ስላ ቤተ ክርስቲያናችን የልዕልና አና ብሩህ ጊዜን እናልማለን፡፡  
ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሕዳሴ ዘመን:: ኢትዮጵያ ታላላቅ ቅዱሳንን ያፈራችበትን ወርቃማ ዘመንን ለመድገም ከአሁን የተሻለ ታላቅ አጋጣሚ ይመጣል ተብሎ መቼም የሚጠብቅ አይሆንም፡፡ ፈር ያጡት ሰርዓቶቻችን መስመር የሚይዙበት ፣ ምንም ስርዓት ያልተሰራላቸው ጉዳዮች አዲስ ስርዓት ተዘርግቶላቸው የወደፊት መጭውን እድል የምትወስንበት ፣ እንደ ግመል ያበጡትን ከፍተኛ ችግሮቻችንን የሚወገዱበት ፣ የምንፈታበት ጊዜ ከዚህ የተለየ አጋጣሚ ምቹ ሊመጣ? የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ወርቃማዎቹ ጊዜያት ዛሬ ላለነው ትውልድ ሲናፈቁን የሚኖሩ ቢሆንም እንዲህ ያሉ ትውልድን የምንፈጥረው እጅ ለእጅ ተያይዘን ተከባብረን በአንዲት ቤተክርስቲያን ያለሰለሰ ጥረት ስናደርግ ፣  ስርዓቶቿን ስናስጠብቅና ስንጠብቅ ፣ ማንም እንዳሻው ሲፈነጭ አይቶ ዝም እየተባለ የሚታይበትን ጊዜ ሲከስም መሆነ ግልጽ ነው፡፡  
በዚህ አጋጣሚ ይህ ጊዜ ካለፈን እና መሠረታዊ ችግሮቻችንን ሳናስተካክል የነበረው ስርዓት አለብኝነት ይቀጥል ብለን ዝም ካልን ግን ምን አልባትም ለቤተክርክስቲያናችን ጥቁር አሻራ አስቀምጠን እንዳልፍ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል፡፡ በተለይ ደግሞ የዘረኝነትና የፍቅረ ነዋይ ችግሮች መጥራት ካልቻሉ አደጋው የከፋ ይሆናል፡፡
የውስጥ ችግሮቻችን ምንም ብዙ ቢሆኑም ትኩረት ወስድን እያንዳንዱ ስርዓት እንዲስተካከል ካደረግን በአንድ ሀሳብና በአንድ ልብ ሆነን ከውጪ ጠላቶቻችን የሚመጣብንን የሰማዕትነት ጊዜያት እየናፈቅን ብሩህ ዘመንን እያየን በቃለ እግዚአብሔር የታነጸ ታላቅ ዜጋ ፣ ትውልድ የምንፈጥርበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡: በዚህ ረገድም የግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን አርአያነት ለእኛም ይህ ተስፋ ይሆናል፡፡

Thursday, September 20, 2012

ቅዱስ ያሬድ ዜማውና 1500ኛ አመት መታሰቢያ ክፍል ሁለት



1500 ዓመት የቅዱስ ያሬድን በዓል ምክነያት በማድረግ በክፍል አንድ ስለ ቅዱስ ያሬድ "ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ዜማውና 1500ኛ አመት መታሰቢያ ክፍል አንድ" በሚል ርእስ አስነብበናችኋል፡፡ ዛሬ ደግሞ በክፍል ሁለት የቅዱስ ያሬድ የዜማ ስልት በሚል ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያን ለጥቁር ሕዝቦች መኩሪያ እንድትሆን ያደረጋት የልጆቿ ሀገር ወዳድነትና ጀግንነትን የተመላው ባህሏ ብቻ ሳይሆን የሃይማኖት፣ የሥነ ዜማ ሀገር መሆኗም መጻሕፍተ ታሪክን ባነበቡ ሊቃውንት አንደበት ብቻ ሳይሆን በማዳመጥ  ትውፊት /ርክክብ/ ለኅብረተሰቡ ኀቡእ ያልሆነ ነገር መሆኑ ነው ፡፡
  ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው። መዝ.74:14 ለኢትዮጵያ ከተሰጡት ታላላቅ ሀብቶች መካከል አንድ በልዩ ስጦታ ከሰማያት ከመላእክት በቀር የትም የማይገኝ እና የተም የሌለ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ስልት ነው፡፡  የቅዱስ ያሬድ የዜማ ስልት ግዕዝ ዕዝልና አራራይ በሚባሉ ሦስት የዜማ መደቦች ይመደባሉ፡፡ የሦስቱ መደቦች የዜማ ድምፃቸው አንድ ሲሆን አንድ መሆናቸው የሥላሴን አንድነት የሚያመለክት ነው ፡፡ የዜማ ስልቶች
  •        ግዕዝ- ግዕዝ ማለት ገአዘ ነፃ ወጣ ማለት ሲሆን በዜማነቱ ሲተረጎም የመጀመሪያ አንደኛ ስልት የቀና ማለት ይሆናል ዜማው ፀባይ ደረቅ ያለና ብዙ እርክርክታ የሌለው ለጉሮሮ ጠንካራ ኃይለኛ በመሆኑ ሊቃውንቱ ደረቅ ዜማ ይሉታል                  
  •    ዕዝል፡- የግዕዝ ድርብና ታዛይ ነው ምሳሌነቱ የወልድ ሲሆን ትርጓሜው ፅኑ ማለት ነው፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ጽንዑ የሆነ መከራን ተቀብሎ እኛን የአዳም ልጆች ማዳኑን ያስረዳናል፡፡ አንድም የመለኮትና የትስብእት ተዋህዶ ረቀቅ ስለሚል  ቀስ በቀስ ሊማሩት እንደሚገባ ያስገነዝባል፡፡
  •       አራራይ- የሚያራራ፣ ጥዑም ልብን የሚመስጥ ማለት ነው፡፡ የዜማው ስልት ልብን የሚያራራ በመሆኑ ስያሜውን አግኝቷል፡፡ ሐዋርያትን ከበዓለ ጴንጤቆስጤ በኋላ ያረጋጋ ያጽናና እና ጥበዓተ ድፍረት ሰጥቶ  ዓለምን እንዲያጣፍጡ ስላደረገ  አራራይ ዜማ   በመንፈስ ቅዱስ ይመሰላል፡፡

Tuesday, September 18, 2012

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ዜማውና 1500ኛ አመት መታሰቢያ ክፍል አንድ



ቅዱስ ያሬድ ከአባቱ ከአብዩድ /ይስሐቅ/ ከእናቱ ከክርስቲና /ታውካልያ/ 505 .. ሚያዚያ 5 ቀን በአክሱም  ተወለደ፡፡ በዚህም መሰረት ታላቁ ቅዱስ ያሬድ በሚመጣው ሚያዝያ አምስት 1500 ዓመት ይሆነዋል ማለት ነው ፡፡ ታዲያ የዚህ ታላቅ አባት ለኢትዮጵያ እና ለቤተ ክርስቲያናችን ካበረከተው ታላቅ የአለም ሀብት አንፃር 1500ኛ አመቱ በታላቅ ድምቀት አመቱን ሙሉ መታሰብ ይኖርበታል ፡፡
መቼም ቢሆን እንዲት ሃገር የራሷ የሆነው ባህሏ / ሥርዓቷ/  የሚያኮራትና ማንነቷንም የሚያንጸባርቅ  በመሆኑ ልትጠብቀውና ከትወልድ ወደ ትውልድ ልታስተላልፈው የባለቤትነት ግዴታዋ ነው ፡፡ በመሆኑም ሀገራችን ኢትዮጵያን ለጥቁር ሕዝቦች መኩሪያ እንድትሆን ያደረጋት የልጆቿ ሀገር ወዳድነትና ጀግንነትን የተመላው ባህሏ ብቻ ሳይሆን የሃይማኖት፣ የሥነ ዜማ ሀገር መሆኗም መጻሕፍተ ታሪክን ባነበቡ ሊቃውንት አንደበት ብቻ ሳይሆን በማዳመጥ  ትውፊት /ርክክብ/ ለኅብረተሰቡ ኀቡእ ያልሆነ ነገር መሆኑ ነው ፡፡
በተጨማሪም ሀገራችን ኢትዮጵያ የዘመናት ዑደት ስፍር ቀምር የራሷን  ዜማ ያደላደለች አፍሪካዊት እመቤት ናት ብንል ጽልመት ሊጋርደው የማይችለው ገሀድ ነው፡፡ 

ይሁን እንጂ እኛ ልጆቿ የትናንቱን ለዛሬ ትውልድ ማበርከት ያልቻልን ይመስላል ፡፡   ለዚህም ነው ትናንት የተነሱ የዜማ ሊቃውንት እነ ሞዛርት ከቅዱስ ያሬድ 1250 ዓመት ብኋላ የተወለዱት በዓለም የዜማ ሊቃውንት ሲባሉ ቀደምት የሆነው ቅዱስ ያሬድ ግን ኢትዮጵያውያን እንኳን ስራውን እንዳንዘክረው ስራዎቹን ተራ ስራ ተደርገው እንዲታዩ የማይፈነቀል ድንጋይ የለም፡፡
አበው ለብዙ ዘመናት ይህን ዜማ  በዜማ ቤቱ፣ በቅኔ ቤቱ በመጻሕፍት ቤቱ እንዳልተጠቀሙበት ሁሉ ዛሬ ግን የአበው ያለህ ብለን  ቅዳሴውን በንባብና በአማረኛ ለውጠን ዜማው እነዲዘነጋ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረግን ነው፡፡ ይህ ግን “የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች” ሳያሠኝ አይቀርም ፡፡ 

Friday, September 14, 2012

መስቀልና እመቤታችን

በዲያቆን ኅብረት የሺጥላ 
  • መግቢያ 
በአንድ ቤተሰብ ውስጥ ለእያንዳንዱ የቤተሰብእ አባል የራሱ የሆነ ቦታ ወይም ደረጃ አለው፡፡ እናት ያላት ቦታ አለ፡፡ አባት ያለው ቦታ አለ፡፡ ልጆች ያላቸው ቦታ ደግሞ ይኖራል፡፡ የልጆች ቦታ እንኳን እንደ እድሜያቸውም ሆነ እንዳላቸው የትምህርት፣ የሥራና የሥነ ምግባር ሕይወት የተለያየ ነው፡፡ የታላቅ ልጅ ቦታ ከታናሽ ይለያል፡፡ይህ ዓይነቱ የመዋቅር ልዩነት በየትም ቦታ ይታያል፡፡ በወታደር ቤት ይህ ልዩነት አለ፡፡ በቢሮና በማናቸውም መድረክ ይህ ዓይነቱ ልዩነት የተጠበቀ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ በአንድ ሰው ውስጥም በአካል ብልቶች መካከል ይህ ልዩነት አለ፡፡ ልዩነቱ የኃላፊነት፣ የወሳኝነትና የአስፈላጊነት መጠንን ይገልጣል፡፡ ይህን ልዩነት ተከትሎ የሚመጣ ነገር ደግሞ አለ፡፡ ይኸውም የክብር ልዩነት ነው፡፡
ንዋያተ ቅድሳትም ሁሉ ክብራቸው የተለያየ ነው፡፡ የሥዕል ክብር ከመስቀል፤ የመስቀል ከታቦት የታቦት ከመንበር፤ የመንበር ከአጎበር፤ የመጻሕፍት ከኩስኩስት፤ የጻሕል ከጽዋዕ ወዘተ የተለያየ ነው፡፡  
ወደ ቅዱሳን ምእመናን ስንመጣ ደግሞ የእግዚአብሔር ልጆች ምእመናን በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር ሲኖሩ የራሳቸው የሆነ አሰላለፍ አላቸው፡፡ ይህም በዕድሜና በሌላ ሥጋዊ መመዘኛ ብቻ ሳይሆን በመንፈሳዊ ሚዛን ነው፡፡
ቅዱሳን አንዳቸው ከአንዳቸው በመንፈሳዊ ጸጋና ማዕርግ፣ በክብርም የተለያዩ ናቸው፡፡ ወንጌል እንደገለጠችው ባለ ሠላሳ ፍሬ አለ፤ ባለ ስልሣ ፍሬ አለ፤ ባለ መቶ ፍሬ ደግሞ አለ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ይህን የማዕርግ ልዩነት ሲያስረዳ ‹‹በክብር አንዱ ኮከብ ከሌላው ኮከብ ይለያልና፡፡›› ብሏል፡፡ (1ቆሮ15.41) አበው ‹‹ከጣት ጣት ይበልጣል›› እንዲሉ፡፡ ስለ ክብርና ልዩነት ይህን ሁሉ ያተትነው መስቀልና እመቤታችን በክብር እኩል ናቸውን የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ መንደርደሪያ እንዲሆነን ነው፡፡

ፍሬዋን ለመብላት




መውተርተር መግተርተር ይኑርህ መታታት
መማረክ እጅ መስጠት ትሁን ለጠላት
ለማሸነፍ ይሁን ሁሌም ፆም ፀሎት



ርዕይ የሌለህ እንዳትሆን ከንቱ
ንደፍ ተልዕኮህን አሳውቅ በብርቱ
ይታይሃልን በጭላንጭል ክፍቱ

Sunday, September 9, 2012

አሮጌውን ሰው አስወግዱ ኤፌ. 4:22

በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው 

 "ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ  በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።" ኤፌ4:22-24


"እንግዲህ አሕዛብ ደግሞ በአእምሮአቸው ከንቱነት እንደሚመላለሱ ከእንግዲህ ወዲህ እንዳትመላለሱ እላለሁ በጌታም ሆኜ እመሰክራለሁ።"ኤፌ4:17

 

" የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።" 1ጴጥ.4:3

Friday, September 7, 2012

ርኅወተ ሰማይ እና ጳጉሜ 3 የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል መታሰቢያ



ርኅወተ ሰማይ በቤተ ክርስቲያናችን ከሚከበሩ ታላላቅ በአላት መካከል አንዱ ሲሆን የሚውለውም ጳጉሜ 3 በየዓመቱ የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ቀን ነው፡፡ ርኅወተ ሰማይ የስሙ ትርጉም የሰማይ መከፈት እንደማለት ሲሆን በክርስቶስ ክርስቲያን የተባሉ ሁሉ ፀሎት፣ ልመናቸው ምልጃቸው የሚያርግበት ከአምላክም የሚወርድበት አለት ነው፡፡ በዚህች እለት ቅዱሳን መላእክት የምእመናንን ልመና መስዋእቱን የሚያሳርጉበት እና የአምላካችንን ምህረት ቸርነት ለሰው ልጆች የሚያወርዱበት እለት ፡:

በዚህች ቀን በሚዝንመው ዝናምም በእግዚአብሔር ቸርነት ብዙ ድውያን ፈውሰ ሥጋ ፈውሰ ነፍስን ያገኛሉ መካኖች ከማየ ፀሎቱ ጠጥተውም ማህፀናቸው ይከፈታል ሌሎች ብዙ ተዓምራትም ይደረግባታል፡፡
ጳጉሜ 3 የሊቃነ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል  መታሰቢያ ነው ፡፡
ቅዱስ ሩፋኤል የጦቢትን ዓይን ያበራና ወለተ ራጉኤልን (ራጉኤልን ልጅ) ተቆራኝቷት ከነበረው ጋኔን ያላቀቃት መሆኑ በመጽሐፈ ጦቢት በስፋት ተገልጿል፡፡
"የእግዚአብሔር ምሥጢር ግን በክብር ሊገለጥ ይገባል እንጂ ሊሰውሩት ስለማይገባ የእኔን ተፈጥሮና ስም ልነግራችሁ እፈልጋለሁ ተፈጥሮዬ መልአክ ነኝ፣ ሥራዬም የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ› ሲል ገለጠላቸው፡፡ እነርሱም ወድቀው የአክብሮት ስግደት ሰገዱለት፡፡" መጽ. ጦቢት::
ጦቢት በፋርስ ንጉሥ በስልምናሶር ዘመን የተማረከ ከነገደ ንፍታሌም የተወለደ ጽኑዕ እሥራኤላዊ ነው፡፡ እግዚአብሔር በስልምናሶር ፊት የመወደድን ግርማና ባለሟልነትን ስለ ሰጠው አለቃ አድርጎ ሾሞት ነበር፡፡ ለወገኖቹ ምጽዋት በመስጠት ሕገ ርትዕን በመሥራት የተጋ ሰው ነበር፡፡ ሐና የምትባል ሚስት አግብቶ አንድ ልጅ ወልዷል፡፡ ስልምናሶር ሞቶ ሰናክሬም በነገሠ ጊዜ ከሹመቱ ስለሻረው ደግሞ ወደ ምድያም መሔድ አልቻለም፡፡