Tuesday, August 30, 2011

‹ቤተክርስትያኒቷ ትዘጋ›› የሚል ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ


‹‹የገሀነም ደጆች አይችሏትም››
ጊዜው ወርሀ ክረምት ነው :: የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፆመ ፍልሰታ ወቅት ሲሆን በቤተክርስትያናችን ህግና ስርዓት መሰረት ይህ ጊዜ ዲያቆናት ፤ ካህናት መነኮሳት ፤ ጳጳሳት እና ምእመናን ለሐዋርያት የተገለፅሽላቸው እናታችን ለእኛም በምህረት አትለይን እያሉ በፆም ፤ በፀሎት ፤ በስግደት የሚለምኑበት ጊዜ ነው፡፡

ቦታው በሐረር መንገድ አዋሽ ሰባትን አልፈው ካለው የጉምሩክ የፍተሻ ጣቢያ ትንሽ ኪሎ ሜትር አለፍ ብሎ ከአሰቦት ገዳም መገንጠያ ሳይደርስ ከዋናው አስፋልት አንድ ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኝ የአባታችን የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተክርስትያን ሲሆን የቦታው ስም ቦርደዴ በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ቤተክርስትያን የሚገኝበት ቦታ ላይ ከ30 የማይበልጡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ሲገኙ በቁጥር ከ40 እና ከ50 እጥፍ ልቀው የሚገኙት ግን ሙስሊም ማህበረሰቦች ናቸው፡፡ ይህ ቦታ ለአንድ አፍታም ቢሆን ከነገር እና ከትንኮሳ እፎይ ያለበት ጊዜ የለም፡፡ ቦታ ድረስ ሄጄ በተመለከትኩበት ጊዜ እዚህ ቦታ ላይ ያለው የሙቀት መጠን ክረምት ሳይል በጋ ከ40 ድግሪ በላይ ስለሆነ ቆሞ ማስቀደስ እንደ እግዚሐብሔር መልካም ፍቃድ ፤ ምህረት ፤ ቸርነት እንጂ እንደ እኛ ብርታትና ጥንካሬ እንዳልሆነ ተረድቻለሁ፡፡

ቤተክርስትያኒቷ አካባቢ ያሉት ምዕመና ጧፍ ፤ እጣን ፤ ዘቢብ እና ንዋየ ቅዱሳትን ማሟላት አቅሙ ስለሌላቸው ይህ ችግር የቀን ተቀን የውስጥ ችግር ችግራቸው ሆኖ አሁንም አሉ ፡፡ የባሰ አታም ነውና  አንድ ጊዜ ቅዳሴ ላይ ወንጌል ለማንበብ ጧፍ አልቆ በኩራዝ የተጠቀሙበት ጊዜም ነበር ፡፡
በአካባቢው የሚገኙ ከአክራሪ ወገን የሚመደቡት የእስልምና ተከታዮች በአካባቢው ላይ ለ24 ሰዓት ያህል ከ4 በሚበልጡ መስኪዶቻቸውን ድምፅ ማውጫ Speaker ወደ ቤተክርስትያን አዙረው ‹‹አላህ ዋክበር›› በሚሉበት ሁኔታ ላይ ምንም ጥያቄ ያላቀረቡት በአካባቢው የሚገኙ  ክርስትያኖች በዓመት አንድ ጊዜ ለ16 ቀናት ብቻ ያለውን የሱባኤ ጊዜ ለሊት ሰዓታት እና ኪዳኑ ፤ ጠዋት ትርጓሜው እና ስብከቱ ፤ ከሰዓት ቅዳሴው ረበሸን ብለው ቤተክርስትያኒቷ እንድትዘጋላቸው  ለአካባቢያቸው ወረዳ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው መጠየቃቸውን አረጋግጠናል፡፡ ይህን ጥያቄ የመስተዳድሩ  ሃላፊ ከሰማ በኋላ ለሚቀጥለው ቀን የቀጠራቸው ሲሆን በሚቀጥለው ቀን ሲመጡ ምንም ምላሽ ስላላገኙ ሓላፊውን በኃይል ከቢሮ ያባረሩት ሲሆን ፡፡ ይህ ጥያቄያቸው የክልሉ መንግስ ጋር እንደደረሰ ፤ አካባቢው ላይ የሚገኙ ክርስትያኖች ጉዳዩን ወደ ፊደራል መንግስት የወሰዱት ሲሆን መንግስት የዛኑ ቀን ማታ አካባቢው ላይ የሚገኙ ፌደራል ፖሊሶች ማታ 3፡00 አካባቢ ወደ አካባቢው በፓትሮል በመምጣት ይህን ጥያቄ የጠየቁትን ሰዎች ግማሽ ያህሉን ለቅመው ወስደው ወደ እስር ቤት የከተቷቸው  ሲሆን የተቀሩትን ግን ሸሽተው አምልጠዋል፡፡ መንግስት ይህን እርምጃ ከወሰደ በኋላ ሁኔታውን በጥቂቱ ያረጋጋ ሲሆን ፡፡ በአሁኑ ወቅት አካባቢው በፊደራል ፖሊስ  እየተጠበቀ ይገኛል::

እኛ በአሁኑ ሰዓት እንትና 18 ገፅ ወቀሳ ፃፈ ፤ ያኛው ሰባኪ አውደ ምህረት ላይ እንዳይቆም ተከለከለ ፤ በዚህ መፅሄት ላይ እንትና መልስ ሰጠ ፤ አንዱ ይቅርታ አለ ሌላኛው ይቅርታ ተቀበለ እያልን ስራ መስራት በሚገባን ወቅት ወሬ ስናራግብ ለቤተክርስትያን መሆን በሚገባን ሰዓት ጊዜያችንን እና አቅማችንን አልባሌ ቦታ ላይ በማዋልና ትርፍ የሌለው ስራ በመስት ላይ እንገኛለን፡፡

አሁንም ጊዜው አልረፈደም ስለ ጥቂት ሰዎች ማውራታችንን አቁመን ስለ ቅድስት ቤተክርስትያን ዘብ እንቁም ዛሬ በሰላማዊ ሰልፍ ይህን የጠየቁ ሰዎች ነገ ምን ማድረግ እንደሚያስቡ ለማስረዳት መምህር ሊያሻን አይገባም፡፡

በዚች ምድር ላይ የምንቆየው እንደ ማቱሳላ 969 ዓመት አለመሆኑን አውቀን በኖርንበት፤በምንኖርበት  ጊዜ ሁሉ ከቤተክርስትያን ጎን ለመቆም ያብቃል፡፡
እግዚሐብሔር ቤተክርስትያንን ይጠብቅ  
by አንድ አድርገኝ

Friday, August 26, 2011

ድንግል ማርያምነኝ ባይዋ ሴት ክስ ሊመሰረትባት ነው

  ..ድንግል ማርያም.. ነኝ ባይዋሴት ክስ ሊመሰረትባት ነው
  • አንዲት የ19 ዓመት ወጣት ሞታለች
  • • እናቴ ከመቃብር በመላዕክት ታጅባ አርጋለች
  • • ሦስት ልጆቿን በመንፈስ ቅዱስ ወለድኳቸው ትላለች፤  ባሏም ተስማምቷል
  • • ህፃናትን ለሦስት ቀናት፤ አዋቂዎችን ለስምንት ቀናትስታፆም ነበር
  • .የሥላሴ መንፈስ በእኔ ላይ አድሯል፤ ከእግዚአብሔር የተላክሁ ማርያም ነኝ.. በሚል ድንኳን በመኖሪያ ቤቷ አካባቢ ተክላ ተከታዮች ስታፈራና እምነቷን ስታስፋፋ የነበረችው ሴት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተካሄደባት ነው፡፡
በአምቦ ከተማ ገላን በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ተወልዳ በ1994 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ የመጣችው ትዕግስት ብርሃኑ ከ1999 ዓ.ም. ጀምሮ ..ማርያም ነኝ.. በሚል ማሳሳቻ ተከታዮችን አፍርታ እንደ ነበር ከፖሊስ የተገኘ ማስረጃ ይጠቁማል፡፡
በዚሁ ዓመት የፋሲካ በዓል ሰሞን ..እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቼ በሦስተኛው ቀን እነሳለሁ.. በማለት ዝግጅት የጀመረችው ትዕግስት፤ የስቅለት ዕለት የእሾህ አክሊልና የምትሰቀልበትን መስቀል አዘጋጅታ ጀርባዋን እንደ ተገረፈች ታውቋል፡፡ በመስቀሉ ላይ መሰቀሏን ያየ ግን አልተገኘም፡፡ በሦስተኛው ቀን ትዕግስት ከሞት ተነሳች ተብሎ ለአካባቢው ህዝብ እንደታየች ምንጮች ይናገራሉ፡፡ የት ደርሳ እንደመጣች የጠየቃት ስለመኖሩ ግን የታወቀ ነገር የለም፡፡ አብረዋት ይኖሩ የነበሩት አባቷ አቶ ብርሃኑ ድርጊቷን አጥብቀው ይቃወሙ እንደነበር የሚናገሩ ምንጮች፤ ጠጥተው ቤት ሲገቡ በጉዳዩ ይነታረኩ እንደነበር ያወሳሉ፡፡ አባቷ ግን የልጃቸውን መለኮታዊ ነኝ ባይነት ማስቆም አልቻሉም፡፡ ትዕግስት ይባሱኑ ..የሥላሴ መልዕክተኛ ድንግል ማርያም ነኝ.. ማለት ጀመረች ይላሉ - ምንጮች፡፡
በዚህ አድራጐቷ የአካባቢው ነዋሪ ሕዝብ ተቃውሞውን በማሰማት ከአካባቢው አባረራት፡፡ ትዕግስት በዚህ ጊዜ ወንጪ ገዳም እንደገባች የገለው ፖሊስ፤ ሀይለገብርኤል ከተባለው ተከታይዋ ሦስተኛ ልጇን እንደ ወለደች ይናገራል፡፡ ከወንድ ጋር ተገናኝታ እንደማታውቅ የምትናገረው ትዕግስት፤ ሦስቱንም ልጆቼን በመንፈስ ቅዱስ ነው የወለድኳቸው ባይ ናት፡፡ የመጀመሪያ ባለቤቷም ይሄንኑ ይመሰክራል - ከእሷ ጋር ስጋዊ ግንኙነት ፈጽሞ እንደማያውቅና ሁለት ልጆቿን በመንፈስ ቅዱስ እንደወለደቻቸው በመናገር፡፡
ትዕግስት በወንጪ ገዳም ሳለች የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ ማለቷን - ገፍታ ቀጠለችበት፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ሌላ ጉድ መከሰቱን የሚናገሩ ምንጮች፤ እናቷ ወ/ሮ ባይሴ ኡዊሳ (በክርስትና ስማቸው ወለተ ሥላሴ) ነሐሴ 25 2000 ዓ.ም. ከቀኑ 9 ሰዓት ሞተው እንደተገነዙ፣ ከዚያም የዚያኑ ዕለት ከምሽቱ 4 ሰዓት ከሞት ተነሱ ተብሎ እንደተወራ ይናገራሉ፡፡ እናት ከሞት የተነሱት ከሰማይ የተላኩትን መልዕክት ለማድረስ እንደሆነ ገልው ..ወ/ሮ ትዕግስት ወይም በክርስትና ስሟ ምስለ ፍቅር ኢየሱስን ስሟት ተብላችኋል.. ካሉ በኋላ በነጋታው ተመልሰው እንደሞቱና ነሐሴ 27 2000 ዓ.ም. የቀብራቸው ሥነ ሥርዓት እንደተፈመ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ ከሁለት ቀን በኋላ ግን መቃብራቸው ተከፍቶ እንዳረጉ ነው ልጃቸው ትዕግስት የተናገረችው፡፡
ነሐሴ 29 2000 ዓ.ም. ሌሊት ላይ ነጐድጓድ መብረቅ ሰምቶ ከጥበቃ ክፍሉ እንደወጣ የሚናገረው የገዳሙ የጥበቃ ሠራተኛ፤ የትዕግስት እናት (በክርስትና ስማቸው ወለተ ሥላሴ) መቃብር ላይ መላዕክት እንዳየ ለፖሊስ ገልል፡፡ በእጁ አብርቶ ይዞት የነበረው ባትሪ መጥፋቱንና መብረቁ ገፍትሮ እንደጣለው ለፖሊስ የገለው የጥበቃ ሠራተኛ፤ በድንጋጤ ወደ ክፍሉ ተመልሶ እንደገባ ተናግሯል፡፡ ሲነጋጋ ሁኔታውን ለማጣራት ወደ መቃብሩ ሲሄድ የወለተ ሥላሴ መቃብር ለሁለት ተከፍሎና መሃሉ ተሰንጥቆ፣ የአስከሬን ሳጥኑ ባዶ ሆኖ ማየቱን በሰጠው ቃል ገልል፡፡
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ትዕግስት ..የዓለም ፍጻሜ ደርሷል፤ ንስሀ ግቡ.. እያለች መስበክ እንደጀመረች ምንጮች ይናገራሉ፡፡
ሴትዮዋ የተቀበሩበት ስፍራ ታጥሮ በሰዎች እየተጐበኘ እንደሆነ የጠቆመው ፖሊስ፤ ሁኔታው የማጣራት ሥራ እንደሚፈልግም ይናገራል፡፡
በረቡዕ ቀን በሬና በግ አርዳ ነዋሪዎች በፆም ቀን ሥጋ እንዲበሉ ማስገደዷ ከነዋሪው ጋር ለተፈጠረው ግጭት መንስኤ ሲሆን፤ የፆም ቀን ቢሆንም አብርሃም ቤትም በሬ ተጥሎ ለሰዎች የመገበው ሐምሌ ሰባት እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፏል በማለት ሐምሌ 7 2002 ዓ.ም. ነዋሪው ሥጋ እንዲበላ፣ ካልበሉ ግን ምድር ተከፍታ እንደምትውጣቸው ታስፈራራ ነበር ተብሏል፡፡ ሥጋውን የበላ ይማራል በማለቷ ግማሹ ነዋሪ ቢበላም ግማሹ አልበላም እንዳለ የጠቆሙ ምንጮች፤ በዚህም ምክንያት ትዕግስት ከአካባቢው ለቅቃ አዲስ አበባ እንደገባች ይናገራሉ፡፡
አዲስ አበባ ከተከታዮቿ አንዷ በሆነችው ሃና ብሩክ በተባለች ግለሰብ መኖሪያ ቤት (ሳር ቤት አካባቢ) ያረፈችው ትዕግስት፤ ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 16 የሚደርሱ ህፃናትና ጐልማሶች አብረዋት ይኖሩ እንደነበር ታውቋል፡፡ ህፃናቱን ለልመና ተግባር ትጠቀምባቸው እንደነበር የጠቆመው ፖሊስ፤ እሷን ተከታይ እንደሆኑና ደረታቸውን በድንጋይ እንዲደልቁ ታደርጋቸው እንደነበር እንዳረጋገጠ አመልክቷል፡፡
አብዛኞቹ ተከታዮቿ ራሳቸውን የማያውቁና ከትክክለኛ አዕምሯቸው እንደተለዩ የሚናገረው ፖሊስ፤ የሴትዬዋ ድርጊት የተጋለጠው ህፃናቱ ለጐረቤት ..እመብርሃን ናት፤ ደሟን እየቀዳች የክርስቶስ ደም ነው እያለች ትሰጠናለች.. ብለው ከተናገሩ በኋላ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪ ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በመጠቆም ወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ በቁጥጥር ስር እንደዋለች ገልል፡፡
በወቅቱ ፍተሻ አለማካሄዱን የጠቆመው ፖሊስ፤ ህፃናቱ የት እንዳሉ እንደማያውቅና ምርመራ ላይ መሆኑን የገለ ሲሆን ከሦስት ዓመት በፊት ከተከታዮቿ አንዷ የነበረችው የ19 ዓመቷ ትዕግስት ያለው ለስምንት ቀን ያለምግብ በመቆየቷ፤ ደረቷን በድንጋይ እንድትደልቅና የተበጠበጠ ምንነቱ ያልታወቀ ቅጠል እንድትጠጣ በመደረጉ ህይወቷ እንዳለፈ ገልል፡፡ የወጣቷን አስከሬን በማውጣት የአሟሟቷን ሁኔታ ለማጣራት ከህክምና ባለሙያዎች ጋር እየተመካከረ እንደሆነም ፖሊስ አክሎ ገልል፡፡
ከወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ ጋር በተያያዘ ትዳራቸው የፈረሰ፣ ንብረታቸውን ያጡ ግለሰቦች እንዳሉም የፖሊስ መረጃ ይጠቁማል፡፡
አዲስ አበባ ቤቴል የተባለው ሰፈር ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አለሚቱ ጉቱ በትዕግስት በደል እንደደረሰባት ቃሏን ለፖሊስ ሰጥታለች፡፡ ቤተሰቧቿ ወደ አምቦ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጉደር ከተማ የወሰዷት፣ ወ/ሮ ትዕግስት በበል ከህመምሽ ትፈውስሻለች በሚል እንደሆነ የተናገረችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ከተጠመቀች በኋላ ከቲቢ ካንሰር ተፈውሰሻል ብለው ህዝብ ተሰብስቦ በቪዲዮ እንደተቀረች ለፖሊስ ገልጻለች፡፡
ከዚህ በኋላ ደግሞ ልጆቼንና ወርቄን ነጥቃኛለች የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ልጆችሽ የእኔ እንጂ ያንቺ አይደሉም መባሏን ትናገራለች፡፡ ..አንድ ቀን የትንሿን ልጄን ጉር ሳበጥር ለምን ነካሻት ተብዬ እስከምዝለፈለፍ ድረስ ተደብዳቤአለሁ.. ትላለች፡፡
ከእኔ የትም አታመልጡም ስለምትል ሁሉም ይፈራታል የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ተከታዮቿ ..እመቤታችን ናት አምልኳት.. እንደሚሉ ትናገራለች፡፡ ..በምስል ታመልካላችሁ፤ ይኸው በአካል መጥታለች አምልኳት.. ይሉናል ብላለች፡፡ በየቀኑ ፆም አለ፤ በቀን አንዴ ንፍሮ እንበላለን ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ፆሙ የአዋቂ ብቻ ሳይሆን ከስድስት ወር ጀምሮ ያለ ህፃንም እንዲፆም ይደረጋል - ለሦስት ቀን ጡት አይሰጠውም ብላለች፡፡
ወ/ሮ ትዕግስት ትምህርት ሃጢያት ነው በሚል አቋም ልጆች እንዳይማሩ እንደምታደርግ አለሚቱ ለፖሊስ ተናግራለች፡፡
የ12 ዓመት ልጄን ከዚህ እንግልት ለማዳን እንጥፋ ብዬው ነበር፤ እሱ ግን ፈርቶ እምቢ አለኝ የምተለው - አለሚቱ፤ የባሰው መከራ የመጣው ግን የ3 ዓመት ልጄ ለ3 ቀን ያለ እህል ውሃ ፆም ፀሎት መያዝ አለበት ስትላት እንደሆነ ተናግራለች፡፡ ትልቁ ልጄ አሻፈረኝ ስላለ ሌላ ሙከራ ባደርግ ይገድሉኛል ብዬ ትንሿን ልጇን ይዛ እንደጠፋች ተናግራለች፡፡ የወንድ ልጇ ነገር ያላስቻላት ወ/ሮ አለሚቱ፤ ተመልሳ ወደ አምቦ መሄዷን ትናገራለች፡፡
ሆኖም ሰው ሁሉ ስለጠላቸው ወደ አዲስ አበባ ሄደዋል ተብላ መመለሷንና ልጇን ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማግኘቷን ገልጻ ለሳምንት ያህል አብሯት ከቆየ በኋላ እንደጠፋ ገልጻለች፡፡ ፖሊስ ልጇን ለሁለተኛ ጊዜ አግኝቶ የሰጣት ቢሆንም ተስማምተው ሊኖሩ እንዳልቻሉ እናት ትናገራለች፡፡ እኔን እንደ እናቱ ሳይሆን እንደ ጠላት ነው የሚያየኝ ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ..ማርያምን ከሰሻት እኔ ካንቺ ጋር አልኖርም.. ይላት እንደነበር ገልጻለች፡፡ ልጄ ..እኛ ምድራዊ አይደለንም፤ ሰማያዊ ነን.. እያለ እሷ የምትናገረውን ሲደግም ነገሩ ከአቅሜ በላይ እንደሆነ ስለገባኝ ወደ እነሱ እንዳይመለስ በማረሚያ ቤት እንዲቆይ ተደርጓል የምትለው እናቱ፤ አሁን ትንሽ ቢሻሻልም፤ እሷን ግን እንደጠላት እንደሚመለከታት ትናገራለች፡፡ ልጄ ጤነኛ አይደለም ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ንብረቴን በሙሉ አጥቼአለሁ ከምንም በላይ የሚጽተኝ ግን ልጄን ማጣቴ ነው ብላለች - እንባዋን እያፈሰሰች፡፡ ወ/ሮ ትዕግስት አበራ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በእስር ላይ ስትሆን ጉዳይዋ ወደ ፍርድ ቤት ተልኮ በጊዜ ቀጠሮ ላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡ወ/ሮ ትዕግስት ለፖሊስ በሰጠችው ቃል ..የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ እኔ ከወንድ ጋር አልተኛሁም፤ ተርፌሳም ማርያም ዮሴፍን ይጠብቃት እንደነበር ጠባቂዬ ነው፤ ሦስት ልጆች ቢኖሩኝም በመንፈስ ነው የወለድኳቸው፤ ይህንን ሁሉ ያደረኩት ሥላሴዎች አዘውኝ ነው፤ አላጠፋሁም.. ብላለች፡፡
ምንጭ አዲስ አድማስ http://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_content&view=article&id=790%3A2011-08-13-09-13-55&catid=76%3Ahot-topic&Itemid=994 በተጨማሪ ፖስት ያደረግነውን ቪዲዮ ይመላከቱ See part 1 http://dekikenabute.blogspot.com/2011/08/blog-post_7994.html?spref=fb part 2 http://www.facebook.com/video/video.php?v=137399669685908&comments&notif_t=video_commen    
part 3 http://www.facebook.com/video/video.php?v=137814382977770&comments&ref=notif&notif_t=video_comment 

Tuesday, August 23, 2011

መለየትን የሚወድ ምኞቱን ይከተላል. ምሳሌ ም .18 ቁ. 1


መለየትን የሚወድ ምኞቱን ይከተላል..
ምሳ ም 18 ቁ 1
"የሞት አያት ማነው?" ብለው በአንድ ወቅት መምህራችን ጠየቁን ሁሉም ለመመለስ አጁን አወጣ፡፡ በጣም ተደነኩ አኔ ግን "ደሞ ለሞትም የዘር ሀረግ አለው እንዴ ?"ብዬ መልሱን ለመስማት ቸኮልኩ፡፡ ብዙዎቻችሁ መልሱን እንደምታውቁት እገምታለሁ፡፡ ግን መልሱን ከማወቃችሁ በፊት ለዚህ ጥያቄ ምን አይነት ምላሽ ትገምቱ ይሆን? አኔ መልሱ እስኪመለስ ባለው ጊዜ በጣም ብዙ ነገር አሰብኩ፡፡ አኔ ካሰብኩት አንዱም መልስ አልነበረም፡፡
በሐዋርያው በቅዱስ ያዕቆብ መልእክት ምዕ 1 ቁ 12-15
"በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።  ማንም ሲፈተን። በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል፤ እግዚአብሔር በክፉ አይፈተንምና፤ እርሱ ራሱስ ማንንም አይፈትንም ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል።  ከዚህ በኋላ ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች፤ ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች።"
ንግዲህ የሞት አያቱ ምኞት ነው ማለት፡፡ መጽሐፍት አንደሚነግሩን
ዘፍ ም 3 ቁ 3-6"… እባብም ለሴቲቱ አላት። ሞትን አትሞቱም፤ ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።
ሔዋን ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ አየች(ተመኘች) ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ወለደች ማለትም ሔዋን ቆርጣ በላች (ሕገ እግዚአብሔርን አፈረሰች) የኃጢአት ደሞዙ (ልጅ) ሞት ነውና ሞት ተፈረደብን፡፡ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በሞቱ ሞትን ሽሮልናል፡፡
አሁን በዚህ ዘመን ምኞታቸውን በመከተል መለያየትን በቤተክርስቲያናችን ለመፍጠር የሚጥሩ አንድና ሁለት አይደሉም፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን እንዳለ የራሳቸውን ክብር አንጂ የቤተክርስቲያን ጉዳይ ምናቸውም ያልሆነ በአጠቃላይ ምኞታቸውን ብቻ የሚከተሉ አባቶችን ከራሳቸው አሳንሰው ራሳቸውን ከፍ አድርገው የቤተክርስቲያን ልጆች እኛ ብቻ ነን የሚሉ (------እኔን ወለደች እገሌን ወለደች -------) ናቸው፡፡ "በልቡ ያለውን ሁሉ መግለጥ ብቻ ይወድዳል እንጂ" ምሳ ም 18 ቁ 2
አነዚህ ሰዎች በጣም የሚገርም ነገራቸው "ለካ ትወዱናላችሁ ለካ ታከብሩናላችሁ ለካ እኛ ብንወድቅ ይህ ሁሉ ሕዝብ ይወድቃል" እያሉ ህዝቡን በምላሳቸው በቃ ምን አለፋችሁ ሁሉም ነገር ምላሳቸው ላይ ነው ያለው፡፡ የቤተክርስቲያንን ፍቅር፤ የሕዝብ ፍቅር ----ወዘተ በምላሳቸው ምላስ ብቻ፡፡ ግን በተጨማሪ ምላሳቸው ከዚህ የተለየም ነገር አለው፤ ስድብ ፡፡ አትሳደቡ ብለው ግን አስተምረውን ያውቃሉ፡፡ ደሞ የት እንደሚሳደቡ ታውቃላቸሁ አውደ ምሕረት ላይ ቆመው፡፡ ምሳሌ (የንፍሮ ቀቃይ ልጅ፣ ……………………..) ከዚህም በላይ እኔ በጣም በእውነት እላችኋለሁ በጣም አዝናለሁ በአውደ ምሕረት ላይ "የጥፋት ርኩሰት ቆሞ ስታዩ ያኔ ሰሚው ያስተውል" 
አነዚህ ሰዎች እውነት አውደ ምሕረት ላይ ራሳቸውን ሳያርሙ፤ የሰደቡትን ሕዝብ ይቅርታ ሳይጠይቁ፤ ሳይማሩ(መቼም ምሥጢራተ ቤተክርስቲያንን ሳያውቁ እንደ ሚያውቁ ሆነው ሲያስተምሩ ሰምተናል ብዬ ነው) ማስተማር አለባቸው ትላላችሁ????
                                                የገዛ ምኞታችንን ከመከተል
የአግዚአብሔርን መልካም ፈቃድ እንድናውቅ
              ፈቃዱንም እንድንተገብር አግዚአብሔር ይርዳን!
የቅዱሳን አባቶቻችን ጸጋ በረከታቸው
ጥርጥር የሌለባት ሃይማኖታቸው
ድል የማትነሳ እምነታቸው
ከአኛ ከሁላችን ጋር ትሁን አሜን!!!!!!!!!

Friday, August 19, 2011

ይቅርታና ይቅር ባይነት

ይቅርታ ወይም ይቅር ባይነት የሰው ልጅ በዚህ ዓለም በሚኖርበት ወቅት በተለያዩ ማኅበራዊ ትስስሮች ወይም ግንኙነቶች አማካኝነት ከሌሎች የማኅበረሰቡ  ክፍሎች ጋር ለሚኖረው ጤናማ የኑሮ ጥምረት ትልቅ ድርሻ አለው ብዬ አምናለሁ። ይቅር መባባል ያለፈ በደልን አጥቦና አስወግዶ ለቀሪው ህይወት አዲስ ልቡናን በመፍጠር ግንኙነታችንን ወደ ተሻለ የኑሮ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል። በአንድ ወቅት በታሪክ አጋጣሚ ተበዳድለው፣ ተቀያይመው፣ ተኮራርፈው ከዚያም ባለፈ ደም ተቃብተው እና ለቂም በቀል ሌት ተቀን በሃሳብም በግብርም ይሯሯጡ የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በልቡናቸው የተቋጠረውን የመጠፋፋት ሕልምና ዕቅድ ወደ ጎን ትተው  አንዱ ካንዱ በጋብቻ እስከመጣመርና አንዱ ላንዱ ዋስ ጠበቃ እስከመሆን ያደርሳቸዋል። በዚሁ መልካም አጋጣሚ ምክንያትም ሊጠፋ የነበረው ሕይወት፣ ሊፈስ የነበረው ደም እና ሊጎድል የነበረው አካል ከጥፋት፣ ከመፍሰስና ከመጉደል ይድናል።


ከዚህም ባለፈ ቂም በቀል በይቅርታ እስካልተደመደመ ድረስ ጥፋቱ መቋጫ የለውም። አንዱ ላለፈ በደሉ አዲስ በደል ሲፈፅም ሌላኛውም አፀፋውን ሲመልስ የሁለቱም ወገኖች በምድር ላይ በሕይወት እስካሉ ድረስ መጠፋፋቱ ይቀጥላል። እንዲህ ዓይነቱ ለይቅርታ ቦታ አለመስጠት በተለይ ከሌላው ዓለም በተለየ መልኩ በእኛ በኢትዮጵያውያን ይብሳል። ምክንያቱ ምን ይሆን? በምጣኔ ሃብት አለማደጋችን፣ በቴክኖሎጂ አለመበልፀጋችን ወይም ገና ያልደረስንበትና ያልተማርነው ዘመናዊ ትምህርት ይኖር ይሆን? ትልቁ መንስዔ ከእነዚህ ምክንያቶች መካከል እንዳልሆነ የምንገነዘበው እነዚህ ምክንያትች ሞልተው የተትረፈረፉላቸው ወገኖቻችን ይባስ ብለው የችግሩ ሰለባ እነሱ መሆናቸው ነው።

ያደግንበት ማኅበረሰብም ሲወርድ ሲዋረድ በመጣው በእትንኩኝ ባይነትና ክንዴን ሳልንተራስ እንዴት እደፈራለሁ? አስተሳሰቡ በደንብ አድርጎ አጥምቆናል። ገና ከእናታችን ማኅፀን ከመውጣታችንም ደም መላሽ ብሎ ስም ያወጣልናል። አንደበታችን እማማ አባባ ማለት ሳይጀምር በቂም በቀል ዲፕሎማ ከቤተሰባችን እና ከአካባቢያችን በከፍተኛ ማዕረግ እንመረቃለን። ከዚያ በኋላ ልክ ግብፃውያን እናቶች ልጆቻቸውን አባይ ሕይወትህ ነው እያሉ እንደሚያሳድጉት ሁሉ ለእኛም የስማችንን ትርጓሜ ከወደፊቱ ስራችን ዕቅድ ጋር እየተነገረን እናድጋለን። ከዚህም በተጨማሪ ሕዝብን እናዝናናበታለን በሚል ሽፋን የሚወጡ ዘፈኖችም የራሳቸው ተፅዕኖ አላቸው። የአንድን ግለሰብ አስተሳሰብ ለመግለፅ እንዲሁም ለግጥሙ ቤት መድፋት እንጂ ጭብጡ በማኅረሰቡ ላይ የሚያመጣውን አሉታዊ ተፅዕኖ ባለማስተዋል የሚዘፈኑ ዘፈኖች አሉ። “ተበድዬስ ይቅርታ አልልም የቀረው ይቅር እንጂ” የሚል ዘፈን ሲያዳምጥና አብሮ ሲያንጎራጉር ያደገ ሰው ለይቅርታ ያለው ቦታ ቢያንስ ኸረ እስከ ጭራሹም ባይኖረው ምን ይደንቃል?

ሁላችንም እንደምናስታውሰው በጀግኖች አባቶቻችን ቆራጥ ተጋዳይነት ለጥቁር ሕዝብ ሁሉ የሚተርፍ የነፃነት ፋና በዓድዋ ተራሮች ተንቦግቡጎ ባልጠበቀውና ባላሰበው መልኩ ድል የተደረገው የኢጣልያ መንግስት ይህንን በዓለም አቀፍ አደባባይ የውርደት ሸማ ያለበሰውን የኢትዮጵያውያን ተጋድሎ ቂም ለመወጣት በተጠቀመው የመርዝ ጋዝ እጅግ ብዙ ወገኖቻችን በመሪር ስቃይ አልፈዋል። እስቲ እነዚህን የነፃነታችን አምድና ለዛሬው እኛነታችን የሕይወትን መስዋዕትነት ከፍለው ስማቸውን በልባችን ፅላት ላይ በወርቅ ማኅተም ያተሙትን ወገኖቻችንን አንድ ጊዜ ቆም ብለን እናስባቸው። 

በዚያን ጊዜ እነደዚያ ያለውን የጭካኔ ርምጃ እንዲወሰድ ያዘዘውን አካል ብናገኘውና እጅና እግሩ ታስሮ ፊት ለፊታችን ቢቀርብልን ምን ዓይነት ርምጃ ይሆን የምንወስድበት? እንደው የትኛውን የቅጣት ዓይነት ብንቀጣው ነው አንጀታችን ቅቤ የሚጠጣው? ምን ዓይነት የአገዳደል ስልት ብንጠቀምና ብንገድለው ነው  ያለፈውን የወገኖቻችን ሕይወት፣ የጎደለውን አካላቸውን እና የፈሰሰውን ደማቸውን ዳግም ማግኘት የምንችለው? ቁርጥርጥ አድርገን ብንፈጨውና ወደ አፈር ብንቀይረው ከዚያም ዳግም እንደ ጭቃ አብኩተን ሰውዬውን ሰርተነው እና ሃይሉ ኖሮን እስትንፋስ እንዲኖረው አድርገን እንደገና ብንቆራርጠው ይህንንም ሂደት ሕይወታቸውን ባጡት ወገኖቻችን ቁጥር ብንደጋግመው ስንቶቹን ይሆን ዳግም በሕይወት የምናገኛቸው? ምንም። እርሱ በከፈተው የክፋትና የጭካኔ ጎዳና አብረነው እንድንጓዝ እና እርሱ ለሰራው ጥፋት በሚጠየቅበት ቦታ ብቸኝነት እንዳይሰማው ከማድረግና ከሚከፈለው ክፍያ ተቋዳሽ ከመሆን ያለፈ ጠቀሜታ የለውም።

ታድያ ቂም በቀሉ ፋይዳው ምንድነው? የመንፈስ እርካታ ይገኝበት ይሆን? በቂም በቀል ደስታና እፎይታን ብሎም እርካታን የሚያገኘው መንፈስ እንዴት ያለው መንፈስ ነው? በእውነት ነፍሳችን በእንደዚህ ያለ ድርጊት ደስታን ታገኝ ይሆን? በጭራሽ። ቂም በቀል ጊዜያዊ የሆነ እርካታን ለስጋችን ይሰጠው ይሆናል እርሱም ቢሆን ቀን አልፎ ቀን ሲተካ ይፀፀታል። ያጣሁትን መልሼ ላላገኝ ይህንን ማድረጌ ምን ጠቀመኝ? ለምንስ የሰነፎችን መንገድ ተከተልኩኝ? እያለ ራሱን መውቀሱ አይቀሬ ነው።  በደልን በበደል፣ ክፋትንም በክፋት፣ ተንኮልንም በተንኮል እንሸፍናለን በሚል የዋህ አስተሳሰብ ታስረን የነገሮችን ውል ከማጥፋት ይልቅ ጥፋትን ተራርሞ ክፍተትን በይቅረታ መሙለቱ የታላቅነትና የአስተዋይነት ብሩሕ ምልክት ነው። ይህ ይቅርታና ይቅር ባይነት መገኛው የት ይሆን?

እንደ እኔ አመለካከት ይቅርታ እና ይቅር ባይነት ምንጩ መንፈሳዊ ሕይወት ነው። ምንም እንኳን ይቅርታ መደራረግ ለስጋዊ ኑሯችንም ታላቅ ጠቀሜታ ቢኖረውም ዋናውና ከዚህ የሚበልጠው ግን መንፈሳዊው ዋጋ ነው። ይህንን መንፈሳዊ ዋጋ ያገኝ ዘንድ ዘወትር የሚተጋ ሰው ልቡናው ለይቅርታ የፈጠነ ነው። በዚህ ምድር በበዳዩ ከተበደለው በደል ይልቅ በሰማይ የሚያገኘው ክብር ሚዛን ይደፋለታል። እዚህ ላይ ግን ሁላችንም ልንገነዘበው የሚገባን ነገር አለ። ይቅር ባይነት ቀላል አይደለም እንደማንኛውም ክብርን እንደሚያጎናፅፍ ተጋድሎ ሁሉ እርሱም ከፍተኛ ተጋድሎ ያሻዋል። በአፋችን ለመናገር እንደሚቀለው ያህል ለመተግበሩ ቀላል አይደለም። ይቅር ለማለት ስናስብ ብዙ ፈተናዎች ፊታችን ይጋረጣሉ። ፈተናው ከራስ ይጀምራል የቤተሰብ ፈተናም አለው እንዲሁም የአካባቢ ተፅዕኖም አለው። እነዚህን ፈተናዎች በድል አድራጊነት መወጣት የሚችል ሰው ነው ይቅር የሚለው እና ሰማያዊውን ክብር ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚያገኘው።

ቁርሾን በሆድ ይዞ ዘወትር መበላላትን፣ መጠፋፋትን እና ልኩን/ለኳን አሳያታለሁ ባይነትን የዘወትር መገለጫው የሆነውን ሰጋችንን ሰማያዊውን ተስፋ አሻግራ ለምትመለከተው ነፍሳችን ስናስገዛ መንፈሳዊነት በሕይወታችን በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደተለኮሰ ሻማ ከሩቅ ያበራል። የዚያን ጊዜ የበደሉንን አካላት መጥተው ይቅርታ እስኪሉን ሳንጠብቅ አስቀድመን ይቅርታን እናደርግላቸዋለን። የሰማያዊው ክብር ባለቤቶች መሆናችንን እናውቃለንና ይቅርታውን ባደረግን ወቅት ከመቼውም ይበልጥ ውስጣችን በሐሴት ይሞላል። የሰላም እንቅልፍም እንተኛለን።

ቸር ያሰማን፤ አሜን።

Thursday, August 18, 2011

በዚህ ዘመን ቅድስት ድንግል ማርያም በስጋ ተገለጠች ቢባሉ ምን ይላሉ?

አይን የማያየው የለም ጆሮም የማይሰማው የለም
በዚህችው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የዋሓንን አማኝ በማሳት በማታለል የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ እና ስርአት ለማጥፋት የሚጥሩ ብዙ የዋህ እንዳሉ የማይካድ እውነታ ነው ይህቺ ቤተ ክርስቲያን ከውጪ ያለችበት ከፍተኛ ፈተና ከፊት ተጋርጦ ሳለ እዚሁ በየገዳማቱ በየአድባራቱ ያሉትን የዋሀንን በፈለጉት ሀሳብ በመስበክ ሕዝቡን እያሳቱ እንዳለ ይህ እውነተኛ ምስክር ነው
  •        ማርያም በዚህ ዘመን ጌታን ለመውለድ ተገለጠች ቢባሉ ምን ይላሉ?
  •          እንደ አይሁድ ገና ጌታ ይወለዳል ቢባሉስ? 
  •      መለኮት ግንቦት 1/1999 ተፀንሶአል ይህንንም በ3 ቀን ሱባኤ ጠይቁ ቢባሉስ?
·         አረ ምኑ ቅጡ ሁሉንም ያድምጡት
በዚህ አይነት መልኩ ደጋፊ ማፍራት ይቻላል? 
see part 2 ተጨማሪ ከፌስ ቡካችን ያድምጡ ይህንም ይጫኑ
see part 3  ተጨማሪ ከፌስ ቡካችን ያድምጡ ይህንም ይጫኑ

ደቂቀ ናቡቴ

አክዓብም ናቡቴ በቤቴ አቅራቢያ ነውና የአትክልት ቦታ አደርገው ዘንድ የወይን ቦታህን ስጠኝ፤ ስለ እርሱም ከእርሱ የተሻለ የወይን ቦታ እሰጥሃለሁ፤ ወይም ብትወድድ ግምቱን ገንዘብ እሰጥሃለሁ ብሎ ተናገረው ናቡቴም አክዓብን የአባቶቼን ርስት እሰጥህ ዘንድ እግዚአብሔር ያርቅልኝ አለው እስከ ሞሞትም በቃ ለርስቱ የናቡቴ ልጆችም ዛሬ እርስታችንን ተዋህዶን ለእነ አድሳት ባዮች አንሰጥም እስከ ደም ጠብታ እንከፍላለን ሲሉ ነው

አባ ሙሴ ጸሊም


አባ ሙሴ ጸሊም በትውልዱ ኢትዮጵያዊ ሲሆን አስቀድሞ በውንብድና ኑሮ ሕይወቱን ይገፋ ነበር፡፡ ሰዎች ከገድሉ የተነሳ ያደንቁታል፡፡እርሱ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበርና እርሱ በሥጋው ጠንካራ ፤ በሥራውም ኃይለኛ ነበር፡፡
አባ ሙሴ ጸሊምም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ፤ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ፡፡ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር ፡፡
አባ ሙሴ ጸሊም ኢትዮጵያዊ
በአስቄጥስ ገዳም ያሉ መነኮሳት እግዚአብሔርን ያውቁታል ፤ ያዩታልም እያሉ ሲነጋገሩ ሰዎችን ሰማቸው፡፡ ያንጊዜም ተነሳ ሰይፉንም ታጥቆ ወደአስቄጥስ ገዳም ሄደ ፤ በደረሰም ጊዜ አባ ኤስድሮስን አገኘው ፤ አባ ኤስድሮስም ፈራው ሙሴ ጸሊምም እውነተኛውን አምላክ ታሳውቁኝና ታስረዱኝ ዘንድ ወደ እናንተ መጣሁ አለው ፡፡ አባ ኤስድሮስም ወደአባ መቃርስ ወስዶ አገናኘው፡፡ እርሱም ተቀብሎ ሃይማኖትን አስተማረው እንዲህም አለው ታግሰህ የማስተምርህን ከጠበቅህ እግዚአብሔርን ታየዋለህ
የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ አመነኮሰው ከብዙዎች ገድለኞች ቅዱሳን ይልቅ ብዙ እና ጽኑዕ ገድልን መጋደል ጀመረ፡፡፡፡በኋላም በገዳመ አስቄጥስ የገዳሙ አበምኔት የነበረው የአባ ኤስድሮስ ደቀ መዝሙር ሆነ፡፡ በአባ መቃርዮስ ምክር ወደ ጴጥራ ሂዶ በተባሕትዎ መኖር ቀጠለ፡፡ ከገድሉ ብዛት የተነሳ አረጋውያን መነኮሳት በሚተኙ ጊዜ ቤቶቻቸውን በመዞር ውሃ መቅጃዎቹን ወስዶ ውሃ ሞልቶ በየቤታቸው ደጃፍ ያኖር ነበር፡፡ ውሃው ከእነርሱ ሩቅ ነበርና እንዲህም እያደረገ በመጋደል ለብዙ ዘመናት ኖረ ፡፡
አባ ሙሴ ጸሊም በበአቱ እያለ የፈቲው ፆር ያሠቃየው ነበር፡፡ ፈተናውን ተቋቁሞ በበአቱ መቀመጥ ስላልቻለ ወደ ገዳሙ አበምኔት ወደ አባ ኤስድሮስ ዘንድ ሄደና ‹በበኣቴ መቀመጥ አልቻልኩም› አለው፡፡ አባ ኤስድሮስም ወደ በኣቱ ተመልሶ በዚያው እንዲጸና መከረው፡፡ ሙሴ ግን ‹ፈጽሞ አልችልም› አለ፡፡ በዚህ ጊዜ አባ ኤስድሮስ ሙሴን ይዞት ከገዳሙ ቅጥር ውጭ አወጣው ከዚያም ወደ ምዕራብ አዞረውና ‹ተመልከት› አለው፡፡ በዚያ አቅጣጫ የአጋንንት መንጋ ለወረራ ሲዘጋጁና ሲንጫጩ አሳየው፡፡ ቀጥሎ ደግሞ ወደ ምሥራቅ እንዲመለከት አደረገውና እልፍ አእላፍ መላእክት ብርሃን ተጐናጽፈው አሳየው፡፡ ከዚያም ‹እነዚህ የብርሃን መላእክት ቅዱሳንን ለመርዳት ከእግዚአብሔር የሚላኩ ናቸው እነዚህ ርኩሳን አጋንንት ደግሞ ቅዱሳንን ለመፈተን የሚዘምቱ ናቸው፡፡ የብርሃን መላእክት ኃይል ከአጋንንት ኃይል ይበልጣሉና ጸንተህ ተጋደል› ሲል መከረው አባ ሙሴም ወደ በኣቱ ተመለሰ፡፡
አባ ሙሴ በገዳመ አስቄጥስ እያለ ከገዳማውያን አንዱ ጥፋት ሠራና ማኅበሩ ለፍርድ ተሰበሰበ፡፡ አባ ሙሴ ግን በጉባኤው ላይ አልነበረም፡፡ ስለዚህ ካህኑ ተልኰ ‹ና. ሁላችንም አንተን እየጠበቅን ነው› አለው፡፡ አባ ሙሴም በሚያፈስስ ከረጢት አሸዋ ሞልቶ ያንንም በጀርባው ተሸክሞ ከኋላው እያፈሰሰ ወደ ጉባኤው አመራ፡፡ ጉባኤተኞቹ ተገርመው ለምን እንደዚህ እንዳደረገ ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹የእኔ ኃጢአቶች በኋላየ እንደዚህ አሸዋ በዝተው ይፈሳሉ፤ ነገር ግን ላያቸው አልቻልኩም ዛሬ ግን በሌላው ላይ ለመፍረድ መጥቻለሁ፡፡› አላቸው፡፡ ይህን ሲሰሙ ዝም አሉ፡፡ ያን ወንድምም በይቅርታ አለፉት፡፡
በሌላ ጊዜ በገዳመ አስቄጥስ ያሉ መነኰሳት ተሰበሰቡና የአባ ሙሴን ትዕግሥት ለመፈተን ሲሉ “ይህ ጥቁር መነኩሴ ለምን እዚህ መጣ “ ብለው ተናገሩት፡፡ እርሱም ዝም አለ፡፡ ጉባኤው ሲበተን “አባ ክፉ ስንናገርህ ምንም ሐዘን አልተሰማህም ነበርን ?” ሲሉ ጠየቁት፡፡ “ተሰምቶኛል፣ ነገር ግን እንዳልናገረው አንደበቴን ተቆጣጠርኩት” አላቸው፡፡
በአንድ ወቅት በገዳመ አስቄጥስ ጾም ታወጀ፡፡ በዚያ ሳምንት አባ ሙሴን ለማየት ከግብጽ ወንድሞች መጡ፡፡ አባ ሙሴም በእንግድነት ተቀበላቸውና ምግብ ያበስልላቸው ጀመር፡፡ የእሳቱን ጢስ የተመለከቱ ጐረቤቶቹ “አባ ሙሴ ትእዛዝ አፍርሶ ምግብ ያበስላል” ብለው ለገዳሙ ሓላፊዎች ተናገሩ፡፡ ሓላፊዎቹም ‹አሁን ተውት ሲመጣ እኛው ራሳችን እናናግረዋለን› አሏቸው፡፡ ሓላፊዎቹም አባ ሙሴን ጠርተው ለምን ምግብን እንዳበሰለ ተረዱ፡፡ በቀዳሚት ሰንበት ማኅበሩ ሁሉ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጣ በአደባባይ ‹አባ ሙሴ ሆይ የሰውን ትእዛዝ አልጠበቅኽም፤ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ (እንግዳ ሆኜ መጥቼ ተቀብላችሁኛል የሚለውን) ግን ጠብቀሃል› ብለው አመሰገኑት፡፡
አንድ ጊዜ የአካባቢው ገዥ ስለ አባ ሙሴ ዝና ሰምቶ ያየው ዘንድ ወደ ገዳመ አስቄጥስ መጣ፡፡ ይህን የሰማው አባ ሙሴ ሸሽቶ ወደ ጫካ ገባ፡፡ በመንገድም ላይ የገዥው መልእክተኞች አገኙትና ‹እባክህ አባ ሙሴ የት እንዳለ በኣቱን አሳየን› አሉት፡፡ ‹ከርሱ ምን ትሻላችሁ፤ እርሱ ኮ ቂላቂል ነው› አላቸው፡፡ ይህን የሰማው የአካባቢው ገዥ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መጣና የሆነውን ሁሉ ለአገልጋዮች ነገራቸው፡፡ ‹ብዙ ሰዎች ስለ አባ ሙሴ ሲያወሩ ሰምቼ ለማግኘት መጥቼ ነበር፤ በመንገድ ላይ ያገኘነው አንድ አረጋዊ ሰው ግን የአባ ሙሴ በኣት የት እንደሆነ ስንጠይቀው ከርሱ ምን ትሻላችሁ እርሱ ኮ ቂላቂል ነው አለን› ብሎ ነገራቸው፡፡ አገልጋዮቹም በጣም ተናደዱና ‹ምን ዓይነት አረጋዊ ሰው ነው ስለ ቅዱሱ ይህን የሚናገር› ብለው ጠየቁት፡፡ ‹ትልቅ፣ ጠቆር ያለ፣ አሮጌ ልብስ የለበሰ ነው› አላቸው፡፡ አገልጋዮቹም ተገርመው ‹ይህማ ራሱ አባ ሙሴ ነው፤ ይህን ያለህ ሊያገኝህ ስላልፈለገ ነው› አሉት፡፡ የአካባቢው ገዥም ከአባ ሙሴ ሁኔታ ከንቱ ውዳሴን ስለ መሸሽ ትልቅ ትምህርት ተምሮ ተመለሰ፡፡
አባ ሙሴ በኣት ሠርቶ ወደ ጴጥራ ሲሄድ በአካባቢው ውኃ ስላልነበረ ተጨንቆ ነበር፡፡ አንድ ድምፅ ‹ሂድ ስለምንም ነገር አትጨነቅ› አለው፡፡ ስለዚህም በዚያ መኖር ጀመረ፡፡ አንድ ቀን በጴጥራ እያለ አበው ሊጐበኙት መጡ፡፡ የነበረችው ውኃ ጥቂት ነበረችና በርሷ ምግባቸውን አበሰለ፡፡ የሚያጠጣቸው ግን አላገኘም፡፡ ስለዚህ ወደ ውጭ እየወጣ ውኃ ይሰጠው ዘንድ እግዚአብሔርን ይለምን ነበር፡፡ በመጨረሻ ዝናብ ዘነበና የውኃ ማጠራቀሚያዎቹን ሁሉ ሞላቸው፡፡ እነዚያ አባቶችም ‹ትወጣና ትገባ የነበረው ለምን እንደሆነ እባክህ ንገረን› አሉት፡፡ ‹እናንተ በእንግድነት ስትመጡ ውኃ አልነበረኝም፣ ስለዚህ ያንተን አገልጋዮች ወደ እኔ ልከሃቸዋል፣ ነገር ግን ውኃ የለኝም፣ ስለዚህ እባክህ ውኃ ስጠኝ እያልኩ እግዚአብሔርን ለመለመን ነበር› አላቸው፡፡
አንድ ወንድም አባ ሙሴን ‹አንድን አገልጋይ ባጠፋው ጥፋት የተነሣ ጌታው መታው፡፡ አገልጋዩ ምን ማለት አለበት?› ብሎ ጠየቀው፡፡ አባ ሙሴም ‹አገልጋዩ ብፁዕ ከሆነ፣ አጥፍቻለሁና ይቅር በለኝ ማለት አለበት፡፡› አለው፡፡ ‹ሌላ አይጠበቅበትምን?› ሲል ያ ወንድም ጠየቀው፡፡ ‹አይጠበቅበትም፣ ለጊዜው ለጥፋቱ ሓላፊነቱን ወስዶ አጥፍቻለሁ ካለ ጌታው ይቅር ይለዋል፡፡ የዚህ ሁሉ ዓለማው በባልጀራ ላይ ላለመፍረድ ነው፡፡ በእውነቱ ጌታችን የግብጽን በኩራት ሁሉ ሲመታ ሰው ያልሞተበት አንድም ቤት አልነበረም› አለና መለሰለት፡፡ ያም ወንድም ‹ምን ማለት ነው?› አለው፡፡ ‹ሁላችንም የየራሳችንን ጥፋቶች ካየን የባልንጀራችንን ለማየት ዕድል አንሰጥም፡፡ በራሱ ቤት ሰው የሞተበት በጐረቤቱ ልቅሶ ለማልቀስ አይሄድም፡፡ ለባልንጀራ መሞት ማለት ለራስ ጥፋት ትኩረት በመስጠት፣ የሌላውን ጥፋት ከቁም ነገር አለመቁጠር ነው፡፡ ማንንም አትጉዳ፣ በማንም ላይ ክፉ አታስብ፣ ክፉ የሚሠራውን ሰው አትናቀው፣ በባልንጀራው ላይ ክፉ በሚሠራ ሰው ላይ አትተማመን፣ በባልንጀራው ላይ ክፉ ከሚሠራ ሰው ጋር አትደሰት፣ ለባልንጀራ መዋቲ መሆን ማለት ይህ ነው፡፡ በማንም ላይ አትማረር፣ ነገር ግን ‹ሁሉንም እግዚአብሔር ያውቃል፡፡› በል፡፡ ከሚያማ ሰው ጋር አትተባበር፣ በሐሜቱም አትደሰት፣ ወንድሙን የሚያማውን ሰውም አትጸየፈው፡፡ አትፍረድ ማለት ትርጉሙ ይህ ነው፡፡ በማንም ላይ የጥላቻ ሓሳብ አይኑርህ፣ ጥላቻ ልብህን እንዲያሸንፈውም አትፍቀድለት፡፡ ባልንጀራውን የሚጠላውን አትጥላው፣ ሰላም ማግኘት ማለት ይህ ነው፡፡
አንድ ጊዜ በገዳመ አስቄጥስ ወንድሞች አብረውት እያሉ አባ ሙሴ ‹ተመልከቱ በርበሮች ገዳማችንን ሊያጠፉ እየመጡ ነው፡፡ ተነሡና ሽሹ› አላቸው፡፡ እነርሱ ግን ‹አባ አንተስ አትሸሽምን?› ሲሉ ጠየቁት፡፡ አባ ሙሴም ‹እኔማ ይህችን ቀን ለብዙ ዘመናት ስጠብቃት ኖሬአለሁ፡፡ ጌታ በወንጌል ‹ሰይፍን የሚያነሡ በሰይፍ ይጠፋሉ› ያለው ቃል (ማቴ. 25.52) ይፈጸማል፡፡› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹እኛም አንሸሽም፣ አብረን እንሞታለን እንጂ› አሉት፡፡ አባ ሙሴም ‹ያ ለእኔ ረብ የለውም፤ ሁሉም ሰው ለየራሱ ይወስን› ብሉ መለሰላቸው፡፡ በዚያ ለነበሩት ሰባት ወንድሞች ‹በርበሮች ወደ ገዳሙ ደጅ እየደረሱ ነው› ብሎ ነገራቸው፡፡ ወዲያውም በርበሮቹ ደርሰው ገዳማውያኑን በሰይፍ መቷቸው፡፡ ከሰባቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ ሸሸና በተቆለለው ሰሌን ውስጥ ተደበቀ፤ ወዲያውም ሰባት አክሊላት ሲወርዱላቸው ተመለከተ፡፡
የአባ ሙሴ ጸሊም በረከት ይደርብን አሜን
ዋቢ ስንክሳር ሠኔ 24
በበረሓው ጉያ ውስጥ

የተለያዩ ጊዜ በጋሻው የፈጸማቸው ስህተቶች