Saturday, August 18, 2012

ደብረ ታቦር


+++++++++++++++እንኳን ለታላቁ ለደብረ ታቦር በአል አደረሳችሁ+++++++++++++

እግዚአብሔርና በሰው ልጆች ግንኙነት ውስጥ ጥልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ድርጊቶች እና ክንውኖች በዓመቱ ውስጥ ቀናት ተመድበውላቸው በበዓላትና በአጽዋማት መልክ ይታሰባሉ፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያን እነዚህን በዓላትና አጽዋማት የምታከብርበት ዓመታዊ መርሐ ግብር እና በበዓላቱና በአጽዋማቱ የሚታሰበውን ነገር አስመልክቶ አባላቶችን የምታስተምርበት ሥርዓተ ትምህርት አላት፡፡ እንደዚህ ባለ መርሐ ግብር ከሚታሰቡት መካከል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመነ ሥጋዌው ያደረጋቸው ነገሮችና ያስተማራቸው ትምህርቶች /ፅንሰት፣ ልደት፣ ጥምቀት፣ ስቅለት፣ ትንሳኤ፣ ዕርገት፣ ደብረ ታቦር፣ምጽአት/ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓላት  /ልደቷ፣ ዕረፍቷ፣ ቤተመቅደስ መግባቷ፣ ድንቅ ተአምራት ያደረገችባቸው ዕለታት/፤፣ የቅዱሳን በዓላት /ልደታቸው፣ ዕረፍታቸው፣ ተአምራት ያደረጉባቸው. . / ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡ ከነዚህ ውስጥ ዋነኛው ደብረ ታቦር ነው 
ትንቢት:-  ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌሥሑ ወይሰብሑ በስምከ ታቦርና አርሞንኤም በስምህ አምነው በተደረገላቸው ነገር ደስ ይላቸዋል፣ ስምህን ያመሰግናሉ፣ ለስምህም ምስጋና ያቀርባሉ፡፡ መዝ 8812

Friday, August 17, 2012

በተለያዩ ቦታዎች ውጥረት ነግሶአል

ኦ እግዚኦ አድኅና ለነፍሰ አርክከ አባ ጳውሎስ 
የብፁዕ ወቅዱስ ዶክተር አቡነ ጳውሎስ ፓትርያሪክ ርእሰ ሊቀ ጳጳስ ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሓይማኖት
የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዘዳንት እና የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዘዳንት የቀብር ስነ ስርዓት የሚፈፀምበት እለት ነሐሴ 17/2004 ሀሙስ ከቀኑ 6.00 ሰዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል መሆኑ ተለፀ::
የጸሎት ስርአቱ የሚጀምረውም ረቡዕ በ16  ከሰዓት ብኋላ በቅድስት ማርያም ፀሎተ ፍትሃት ይጀምራል ከዚያም   ሀሙስ በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ከቅዳሴ ብኋላም የተለያዩ መርሃግብሮች ተደርገው አስከሬናቸው ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሐይማኖት ከተቀበሩበት አጠገብ ሥርዓተ ቀብራቸው ይፍፀማል::

ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ እስኪመረጥ ድረስ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ቋሚ ሲኖዶሱን በመሰብሰብ በሐላፊነት ይቆያሉ::

በተለያዩ ቦታዎች ውጥረት ነግሶአል፡-

Thursday, August 16, 2012

አወዛጋቢዋ ድንግል ማርያም ነኝ ባይዋ ሴት በድጋሚ ወደ ዜና ብቅ አለች

  • በአዲስ አበባ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በግድያ ወንጀል እና በተለያዩ ክሶች አቃቤ ሕግ ከሷታል፡፡
  • በሌላ በኩል ከአዲስ አበባ ውጪ በፊቼ ክስ ተመስርቶባታል፡:
  • ተከታዮቿ በአዳዲስ ምልምሎችም ከበፊቱ በዝተዋል፡፡
  • ተከታዮቿ ከደብረ ሊባኖስ  መስቀል ቤተ  በመግባት እና ደብሩ ቅዳሴ ላይ እያለ ቅዱሳኑን እና መስቀሉን በመሳደባቸው ግጭት  እና ብጥብጥ ፈጥረዋ፡፡ 
ከሰማናቸው በጣም አስገራሚ እና አሳዛኙ ከስተቶች መካከል የዚህች ድንግል ማርያም ነኝ ባይ  ሴት ጉዳይ ከሁሉም አስገራሚ እና አሳዛኝ እንዲሁ በደፈናው ተከታይ ማፍራት እንደሚቻልና የዋሐንን በቀላሉ በመያዝ እንደሚጠቀሙባቸው ያሳየል፡፡ ለካ በቀላሉ የሚታለል ሰው በዝቷልና ያሰኛል፡፡

የፓትርያሪኩ እረፍት


ብፁዕ ወቅዱስ ዶክተር አቡነ ጳውሎስ ፓትርያሪክ ርእሰ ሊቀ ጳጳስ ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሓይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዘዳንት እና የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዘዳንት ንጋት ላይ አርፈዋል፡፡
እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር! 
አባ ጳውሎስ ባደረባቸው ህመም ዛሬ ነሐሴ 10 ከንጋቱ 11.00 ሰዓት ላይ በ76 ዓመታቸው አርፈዋል፡፡

ባለፈው እሁደ ነሐሴ 6 2004 የመጨረሻ የቅዳሴ ሰነስርአቱን በቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የመሩት ብፁዕነታቸው ቤተ ክርስቲያናችንንም በፓትርክና ለ20 አመታት ያህል ሲገለግሉ ነበር፡፡

Wednesday, August 15, 2012

ሰበር ዜና አቡነ ጳውሎስ ማረፋቸው ተረጋገጠ


ሰበር ዜና አቡነ ጳውሎስ  ማረፋቸው ተረጋገጠ፡፡ ዛሬ ሌሊት ዐረፉ:: ትላንት ከወትሮው በተለየ ህመማቸው አደገኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ ምክንያት  ባልቻ ሆስፒታል ገብተው እንደነበረና ዶክተሮቹም ህይወታቸውን ለማትረፍ ከፍተኛ ርብርብ ላይ መሆናቸውን የሰማን ሲሆን አሁን ደግሞ ማረፋቸውን አረጋግጠናል፡፡ 

በገዳማት ላይ እየተከሰተ ባለው ጥቃት በተመለከተ የተደረገው ስብሰባ

ባለፈው እንዳስነበብናችሁ በገዳማት ላይ እየተከሰተ ባለው ጥቃት በተመለከተ ስብሰባ

መጠራቱ ይታወሳል::   በተለያዩ ሃሳቦች ላይ ተወያይቷል ከሴቭ ዋልደባ ያገኘነውን መረጃ እንደሚከተለው ነው ከሴቭ ዋልደባ ያገኘነውን መረጃ እንደሚከተለው ነው 

የዋልድባ ጉዳይ ዋና መነጋገሪያው ነበር

  • ዋልድናን ለመታደግ ምን እንርዳ?
  • ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ የቤተክርስቲያን ህልውና ለማስከበር መተባበር ግድ ይለናል
  • የዋሽንግተን ዲሲ ካህናት ለምን አይተባበሩም
  • ጥቂት ካህናት ዋልድባ ምንም እንዳልተነካ የሃሰት መረጃዎችን ለሰው እያስተላለፉ ይገኛሉ

ራሱን “ጉባኤ አርድእት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ” ብሎ የሚጠራውን ቡድን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አገደ


በጠቅላይ ቤተ ክህነት አካባቢ ራሱንጉባኤ አርድእት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶብሎ የሰየመውን ቡድን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ /ቤት የእገዳ ደብዳቤ ጣለበት፡፡ የጉባኤው መስራቾች ነን ባዮች እነ ንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ ፡ ቆሞስ አባ ሠረቀብርሃን ወልደ ሳሙኤል ፡ሊቀ ስዩማን ኃይለ ጊዮርጊስ ጥላሁን እና ሌሎች 27 የሚሆኑ ሲሆ ጉባኤውን እያደራጁ የሚገኙ ግለሰቦች አብዛኛዎቹ በሚሠሩባቸው ቦታዎች ተቀባይነት እያጡ የመጡ ግለሰቦች እንደሆኑ ለመረዳት ችለናል::   

Tuesday, August 14, 2012

በእንተ ስማ ለማርያም ስለ እመ አምላክ

 በእንተ ስማ ለማርያም ስለ እመ አምላክ
 ቤተ ክርስቲያን ሰማይና ምድር ከመፈጠራቸው በፊት ነበረች። ዓለማት ከተፈጠሩ በኋላ በዓለመ መላእክት፣ በዓለመ መሬት በሕገ ልቡና እና በሕገ ኦሪት እግዚአብሔር በመረጣቸው ነቢያትና ካህናቱ አማካኝነት ሰዎችን ከእግዚአብሔር ጋር ስታገናኝ ኖራለች። በዘመነ ሐዲስ ደግሞ በደመ ክርስቶስ ተዋጅታ ሕገ ወንጌልን ስትናኝ እና አምልኮተ እግዚአብሔርን ስታስፋፋ ኖራለች። በእነዚህ አዝማናት ሁሉ ስለ እርሷ ሳይፈሩና ሳያፍሩ አንገታቸውን ለሰይፍ፣ ጀርባቸውን ለግርፋት፣ እግራቸውን ለሰንሰለት የሰጡላት፣ በብዙ መከራዎች የተጋደሉላትን አበው፣ ነቢያት፣ ሐዋርያት፣ ሰማዕታትን እና በእነርሱ መንገድ የተጓዙ ብዙ ሊቃውንትን አፍርታለች (ዕብ ፲፩)።