Saturday, December 15, 2012

በዋልድባ ስቃዩ እና እንግልቱ ቀጥሏል

በዋልድባ ገዳም አካባቢ መንግሥት የተለያየ ሙከራዎችን እያደረገ እንደሚገኝ እና በገዳማውያኑ ላይ ስቃዩን እንደቀጠለ ይነገራል። ባለፈው ወር ላይ የገዳሙን አባቶች ጥቂት የመንግሥት ባለሥልጣናት ሰብስበው እንዳነጋገሯቸው እና ለጥር ፬ ቀን ቀጠሮ ሰጥተዋቸው እንደተበተነ ይታወሳል። በመጪው ጥር ፬ ቀን ምን ሊመጣ እንደሚችል በገዳማውያኑ ላይ ሊደርስባቸው የሚችሉትን፣ እንደ መንግሥት ባለሥልጣኖች አባባል በጥር ፬ ቀን በሚደረገው ስብሰባ ላይ የመንግሥት ተወካዮች ለገዳሙ አባቶች "ለቦታው ካሳ ተቀበሉ አለበለዚያ ሌላ ነገር ይመጣል" በማለት ገዳማውያኑን ለማስፈራራት ቢሞክሩም፥ ገዳማውያኑም "ሞትም ቢመጣ እኛ የአባቶቻችንን ርስት አሳልፈን አንሰጥም፣ እኛን ገላችሁ ሥራችሁን መስራት ትችላላችሁ" በሚል ሁኔውን እየተጠባበቁ ይገኛሉ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ መንግሥት የገዳሙን ይዞታ የቋርፍ (የገዳማውያኑ ምግብ) የሚመረትበትን ቦታ ወስዶ ስላረሰው ገዳማውያኑ በከፍተኛ የረሃብ አደጋ ተጋልጠዋል፥ ከዚህ በተጨማሪ የገዳማውያኑ የሳር ቤት ክዳን ባለው ቤት ላይ ተባይ በማፍራቱ ገዳማውያኑን ለተጨማሪ አደጋ ተዳርገዋል። ከዋልድባ ዳልሻህ ኪዳነ ምሕረት የአንድነት ገዳም ሦስት የመነኮሳይት ቡድን ወደ አዲስ አበባ ተልኮ የአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለመጠየቅ መጥተው እንደነበር እና ነገር ግን ከቤተክህነቱም ምንም ዓይነት ድጋፍ ሳይደረግላቸው መነኮሳይቱ ወደ ባዕታቸው ለመመለስ ችለዋል። 

በትላንቱ ታሕሳሥ ፭ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. በESAT Radio ዘገባ መሰረት፡-
  • በገዳሙ ስቃዩ ተባብሷል፡፡
  • በገዳሙ በስራ ላይ የነበረው የቻይና ኩፓንያ ከቦታው ወጥቶ ሌላ የህንድ ኩፓንያ ተተክቷል፡፡ አንድ ቻያናዊ መሞቱ ተነግሯል፡፡
  • በዋልድባ ገዳም መነኮሳት ላይ እየደረሰ ያለው ስቃይም እንደ አዲስ አጠናክሮ ቀጥሏል
  • መረጃ ለተለያዩ ሚዲያዎች ሲሰጠ የነበሩትን አባት እየተፈለጉ ነው ያሉት ፡፡ እሳቸውንም ላገኘ በሽልማትነት የኮንዶሚኒየም ቤት መንግስት  እንደሚሸልም አስታውቋል፡፡
ራዲዮ ፕሮግራሙ


 

2 comments:

  1. Whoa! This blog looks exactly like my old one! It's on a completely different topic but it has pretty much the same layout and design. Superb choice of colors!
    Also visit my page kissimmeepublic golf courses

    ReplyDelete
  2. Hey! Someone in mу Facеbooκ gгoup shаred thіs website with uѕ sο I
    cаme to give it a looκ. I'm definitely loving the information. I'm bοοk-marκing and ωill be tωeеtіng this tο
    my folloωers! Wondeгful blοg аnd еxcellent
    stylе аnd design.

    My wеbѕite ... Reiki master Training
    my site > physiotherapy

    ReplyDelete