Tuesday, August 30, 2011

‹ቤተክርስትያኒቷ ትዘጋ›› የሚል ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ


‹‹የገሀነም ደጆች አይችሏትም››
ጊዜው ወርሀ ክረምት ነው :: የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፆመ ፍልሰታ ወቅት ሲሆን በቤተክርስትያናችን ህግና ስርዓት መሰረት ይህ ጊዜ ዲያቆናት ፤ ካህናት መነኮሳት ፤ ጳጳሳት እና ምእመናን ለሐዋርያት የተገለፅሽላቸው እናታችን ለእኛም በምህረት አትለይን እያሉ በፆም ፤ በፀሎት ፤ በስግደት የሚለምኑበት ጊዜ ነው፡፡

ቦታው በሐረር መንገድ አዋሽ ሰባትን አልፈው ካለው የጉምሩክ የፍተሻ ጣቢያ ትንሽ ኪሎ ሜትር አለፍ ብሎ ከአሰቦት ገዳም መገንጠያ ሳይደርስ ከዋናው አስፋልት አንድ ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኝ የአባታችን የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተክርስትያን ሲሆን የቦታው ስም ቦርደዴ በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ቤተክርስትያን የሚገኝበት ቦታ ላይ ከ30 የማይበልጡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ሲገኙ በቁጥር ከ40 እና ከ50 እጥፍ ልቀው የሚገኙት ግን ሙስሊም ማህበረሰቦች ናቸው፡፡ ይህ ቦታ ለአንድ አፍታም ቢሆን ከነገር እና ከትንኮሳ እፎይ ያለበት ጊዜ የለም፡፡ ቦታ ድረስ ሄጄ በተመለከትኩበት ጊዜ እዚህ ቦታ ላይ ያለው የሙቀት መጠን ክረምት ሳይል በጋ ከ40 ድግሪ በላይ ስለሆነ ቆሞ ማስቀደስ እንደ እግዚሐብሔር መልካም ፍቃድ ፤ ምህረት ፤ ቸርነት እንጂ እንደ እኛ ብርታትና ጥንካሬ እንዳልሆነ ተረድቻለሁ፡፡

ቤተክርስትያኒቷ አካባቢ ያሉት ምዕመና ጧፍ ፤ እጣን ፤ ዘቢብ እና ንዋየ ቅዱሳትን ማሟላት አቅሙ ስለሌላቸው ይህ ችግር የቀን ተቀን የውስጥ ችግር ችግራቸው ሆኖ አሁንም አሉ ፡፡ የባሰ አታም ነውና  አንድ ጊዜ ቅዳሴ ላይ ወንጌል ለማንበብ ጧፍ አልቆ በኩራዝ የተጠቀሙበት ጊዜም ነበር ፡፡
በአካባቢው የሚገኙ ከአክራሪ ወገን የሚመደቡት የእስልምና ተከታዮች በአካባቢው ላይ ለ24 ሰዓት ያህል ከ4 በሚበልጡ መስኪዶቻቸውን ድምፅ ማውጫ Speaker ወደ ቤተክርስትያን አዙረው ‹‹አላህ ዋክበር›› በሚሉበት ሁኔታ ላይ ምንም ጥያቄ ያላቀረቡት በአካባቢው የሚገኙ  ክርስትያኖች በዓመት አንድ ጊዜ ለ16 ቀናት ብቻ ያለውን የሱባኤ ጊዜ ለሊት ሰዓታት እና ኪዳኑ ፤ ጠዋት ትርጓሜው እና ስብከቱ ፤ ከሰዓት ቅዳሴው ረበሸን ብለው ቤተክርስትያኒቷ እንድትዘጋላቸው  ለአካባቢያቸው ወረዳ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው መጠየቃቸውን አረጋግጠናል፡፡ ይህን ጥያቄ የመስተዳድሩ  ሃላፊ ከሰማ በኋላ ለሚቀጥለው ቀን የቀጠራቸው ሲሆን በሚቀጥለው ቀን ሲመጡ ምንም ምላሽ ስላላገኙ ሓላፊውን በኃይል ከቢሮ ያባረሩት ሲሆን ፡፡ ይህ ጥያቄያቸው የክልሉ መንግስ ጋር እንደደረሰ ፤ አካባቢው ላይ የሚገኙ ክርስትያኖች ጉዳዩን ወደ ፊደራል መንግስት የወሰዱት ሲሆን መንግስት የዛኑ ቀን ማታ አካባቢው ላይ የሚገኙ ፌደራል ፖሊሶች ማታ 3፡00 አካባቢ ወደ አካባቢው በፓትሮል በመምጣት ይህን ጥያቄ የጠየቁትን ሰዎች ግማሽ ያህሉን ለቅመው ወስደው ወደ እስር ቤት የከተቷቸው  ሲሆን የተቀሩትን ግን ሸሽተው አምልጠዋል፡፡ መንግስት ይህን እርምጃ ከወሰደ በኋላ ሁኔታውን በጥቂቱ ያረጋጋ ሲሆን ፡፡ በአሁኑ ወቅት አካባቢው በፊደራል ፖሊስ  እየተጠበቀ ይገኛል::

እኛ በአሁኑ ሰዓት እንትና 18 ገፅ ወቀሳ ፃፈ ፤ ያኛው ሰባኪ አውደ ምህረት ላይ እንዳይቆም ተከለከለ ፤ በዚህ መፅሄት ላይ እንትና መልስ ሰጠ ፤ አንዱ ይቅርታ አለ ሌላኛው ይቅርታ ተቀበለ እያልን ስራ መስራት በሚገባን ወቅት ወሬ ስናራግብ ለቤተክርስትያን መሆን በሚገባን ሰዓት ጊዜያችንን እና አቅማችንን አልባሌ ቦታ ላይ በማዋልና ትርፍ የሌለው ስራ በመስት ላይ እንገኛለን፡፡

አሁንም ጊዜው አልረፈደም ስለ ጥቂት ሰዎች ማውራታችንን አቁመን ስለ ቅድስት ቤተክርስትያን ዘብ እንቁም ዛሬ በሰላማዊ ሰልፍ ይህን የጠየቁ ሰዎች ነገ ምን ማድረግ እንደሚያስቡ ለማስረዳት መምህር ሊያሻን አይገባም፡፡

በዚች ምድር ላይ የምንቆየው እንደ ማቱሳላ 969 ዓመት አለመሆኑን አውቀን በኖርንበት፤በምንኖርበት  ጊዜ ሁሉ ከቤተክርስትያን ጎን ለመቆም ያብቃል፡፡
እግዚሐብሔር ቤተክርስትያንን ይጠብቅ  
by አንድ አድርገኝ

Friday, August 26, 2011

ድንግል ማርያምነኝ ባይዋ ሴት ክስ ሊመሰረትባት ነው

  ..ድንግል ማርያም.. ነኝ ባይዋሴት ክስ ሊመሰረትባት ነው
  • አንዲት የ19 ዓመት ወጣት ሞታለች
  • • እናቴ ከመቃብር በመላዕክት ታጅባ አርጋለች
  • • ሦስት ልጆቿን በመንፈስ ቅዱስ ወለድኳቸው ትላለች፤  ባሏም ተስማምቷል
  • • ህፃናትን ለሦስት ቀናት፤ አዋቂዎችን ለስምንት ቀናትስታፆም ነበር
  • .የሥላሴ መንፈስ በእኔ ላይ አድሯል፤ ከእግዚአብሔር የተላክሁ ማርያም ነኝ.. በሚል ድንኳን በመኖሪያ ቤቷ አካባቢ ተክላ ተከታዮች ስታፈራና እምነቷን ስታስፋፋ የነበረችው ሴት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተካሄደባት ነው፡፡
በአምቦ ከተማ ገላን በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ውስጥ ተወልዳ በ1994 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ የመጣችው ትዕግስት ብርሃኑ ከ1999 ዓ.ም. ጀምሮ ..ማርያም ነኝ.. በሚል ማሳሳቻ ተከታዮችን አፍርታ እንደ ነበር ከፖሊስ የተገኘ ማስረጃ ይጠቁማል፡፡
በዚሁ ዓመት የፋሲካ በዓል ሰሞን ..እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ሞቼ በሦስተኛው ቀን እነሳለሁ.. በማለት ዝግጅት የጀመረችው ትዕግስት፤ የስቅለት ዕለት የእሾህ አክሊልና የምትሰቀልበትን መስቀል አዘጋጅታ ጀርባዋን እንደ ተገረፈች ታውቋል፡፡ በመስቀሉ ላይ መሰቀሏን ያየ ግን አልተገኘም፡፡ በሦስተኛው ቀን ትዕግስት ከሞት ተነሳች ተብሎ ለአካባቢው ህዝብ እንደታየች ምንጮች ይናገራሉ፡፡ የት ደርሳ እንደመጣች የጠየቃት ስለመኖሩ ግን የታወቀ ነገር የለም፡፡ አብረዋት ይኖሩ የነበሩት አባቷ አቶ ብርሃኑ ድርጊቷን አጥብቀው ይቃወሙ እንደነበር የሚናገሩ ምንጮች፤ ጠጥተው ቤት ሲገቡ በጉዳዩ ይነታረኩ እንደነበር ያወሳሉ፡፡ አባቷ ግን የልጃቸውን መለኮታዊ ነኝ ባይነት ማስቆም አልቻሉም፡፡ ትዕግስት ይባሱኑ ..የሥላሴ መልዕክተኛ ድንግል ማርያም ነኝ.. ማለት ጀመረች ይላሉ - ምንጮች፡፡
በዚህ አድራጐቷ የአካባቢው ነዋሪ ሕዝብ ተቃውሞውን በማሰማት ከአካባቢው አባረራት፡፡ ትዕግስት በዚህ ጊዜ ወንጪ ገዳም እንደገባች የገለው ፖሊስ፤ ሀይለገብርኤል ከተባለው ተከታይዋ ሦስተኛ ልጇን እንደ ወለደች ይናገራል፡፡ ከወንድ ጋር ተገናኝታ እንደማታውቅ የምትናገረው ትዕግስት፤ ሦስቱንም ልጆቼን በመንፈስ ቅዱስ ነው የወለድኳቸው ባይ ናት፡፡ የመጀመሪያ ባለቤቷም ይሄንኑ ይመሰክራል - ከእሷ ጋር ስጋዊ ግንኙነት ፈጽሞ እንደማያውቅና ሁለት ልጆቿን በመንፈስ ቅዱስ እንደወለደቻቸው በመናገር፡፡
ትዕግስት በወንጪ ገዳም ሳለች የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ ማለቷን - ገፍታ ቀጠለችበት፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ ሌላ ጉድ መከሰቱን የሚናገሩ ምንጮች፤ እናቷ ወ/ሮ ባይሴ ኡዊሳ (በክርስትና ስማቸው ወለተ ሥላሴ) ነሐሴ 25 2000 ዓ.ም. ከቀኑ 9 ሰዓት ሞተው እንደተገነዙ፣ ከዚያም የዚያኑ ዕለት ከምሽቱ 4 ሰዓት ከሞት ተነሱ ተብሎ እንደተወራ ይናገራሉ፡፡ እናት ከሞት የተነሱት ከሰማይ የተላኩትን መልዕክት ለማድረስ እንደሆነ ገልው ..ወ/ሮ ትዕግስት ወይም በክርስትና ስሟ ምስለ ፍቅር ኢየሱስን ስሟት ተብላችኋል.. ካሉ በኋላ በነጋታው ተመልሰው እንደሞቱና ነሐሴ 27 2000 ዓ.ም. የቀብራቸው ሥነ ሥርዓት እንደተፈመ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ ከሁለት ቀን በኋላ ግን መቃብራቸው ተከፍቶ እንዳረጉ ነው ልጃቸው ትዕግስት የተናገረችው፡፡
ነሐሴ 29 2000 ዓ.ም. ሌሊት ላይ ነጐድጓድ መብረቅ ሰምቶ ከጥበቃ ክፍሉ እንደወጣ የሚናገረው የገዳሙ የጥበቃ ሠራተኛ፤ የትዕግስት እናት (በክርስትና ስማቸው ወለተ ሥላሴ) መቃብር ላይ መላዕክት እንዳየ ለፖሊስ ገልል፡፡ በእጁ አብርቶ ይዞት የነበረው ባትሪ መጥፋቱንና መብረቁ ገፍትሮ እንደጣለው ለፖሊስ የገለው የጥበቃ ሠራተኛ፤ በድንጋጤ ወደ ክፍሉ ተመልሶ እንደገባ ተናግሯል፡፡ ሲነጋጋ ሁኔታውን ለማጣራት ወደ መቃብሩ ሲሄድ የወለተ ሥላሴ መቃብር ለሁለት ተከፍሎና መሃሉ ተሰንጥቆ፣ የአስከሬን ሳጥኑ ባዶ ሆኖ ማየቱን በሰጠው ቃል ገልል፡፡
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ትዕግስት ..የዓለም ፍጻሜ ደርሷል፤ ንስሀ ግቡ.. እያለች መስበክ እንደጀመረች ምንጮች ይናገራሉ፡፡
ሴትዮዋ የተቀበሩበት ስፍራ ታጥሮ በሰዎች እየተጐበኘ እንደሆነ የጠቆመው ፖሊስ፤ ሁኔታው የማጣራት ሥራ እንደሚፈልግም ይናገራል፡፡
በረቡዕ ቀን በሬና በግ አርዳ ነዋሪዎች በፆም ቀን ሥጋ እንዲበሉ ማስገደዷ ከነዋሪው ጋር ለተፈጠረው ግጭት መንስኤ ሲሆን፤ የፆም ቀን ቢሆንም አብርሃም ቤትም በሬ ተጥሎ ለሰዎች የመገበው ሐምሌ ሰባት እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፏል በማለት ሐምሌ 7 2002 ዓ.ም. ነዋሪው ሥጋ እንዲበላ፣ ካልበሉ ግን ምድር ተከፍታ እንደምትውጣቸው ታስፈራራ ነበር ተብሏል፡፡ ሥጋውን የበላ ይማራል በማለቷ ግማሹ ነዋሪ ቢበላም ግማሹ አልበላም እንዳለ የጠቆሙ ምንጮች፤ በዚህም ምክንያት ትዕግስት ከአካባቢው ለቅቃ አዲስ አበባ እንደገባች ይናገራሉ፡፡
አዲስ አበባ ከተከታዮቿ አንዷ በሆነችው ሃና ብሩክ በተባለች ግለሰብ መኖሪያ ቤት (ሳር ቤት አካባቢ) ያረፈችው ትዕግስት፤ ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 16 የሚደርሱ ህፃናትና ጐልማሶች አብረዋት ይኖሩ እንደነበር ታውቋል፡፡ ህፃናቱን ለልመና ተግባር ትጠቀምባቸው እንደነበር የጠቆመው ፖሊስ፤ እሷን ተከታይ እንደሆኑና ደረታቸውን በድንጋይ እንዲደልቁ ታደርጋቸው እንደነበር እንዳረጋገጠ አመልክቷል፡፡
አብዛኞቹ ተከታዮቿ ራሳቸውን የማያውቁና ከትክክለኛ አዕምሯቸው እንደተለዩ የሚናገረው ፖሊስ፤ የሴትዬዋ ድርጊት የተጋለጠው ህፃናቱ ለጐረቤት ..እመብርሃን ናት፤ ደሟን እየቀዳች የክርስቶስ ደም ነው እያለች ትሰጠናለች.. ብለው ከተናገሩ በኋላ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪ ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በመጠቆም ወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ በቁጥጥር ስር እንደዋለች ገልል፡፡
በወቅቱ ፍተሻ አለማካሄዱን የጠቆመው ፖሊስ፤ ህፃናቱ የት እንዳሉ እንደማያውቅና ምርመራ ላይ መሆኑን የገለ ሲሆን ከሦስት ዓመት በፊት ከተከታዮቿ አንዷ የነበረችው የ19 ዓመቷ ትዕግስት ያለው ለስምንት ቀን ያለምግብ በመቆየቷ፤ ደረቷን በድንጋይ እንድትደልቅና የተበጠበጠ ምንነቱ ያልታወቀ ቅጠል እንድትጠጣ በመደረጉ ህይወቷ እንዳለፈ ገልል፡፡ የወጣቷን አስከሬን በማውጣት የአሟሟቷን ሁኔታ ለማጣራት ከህክምና ባለሙያዎች ጋር እየተመካከረ እንደሆነም ፖሊስ አክሎ ገልል፡፡
ከወ/ሮ ትዕግስት ብርሃኑ ጋር በተያያዘ ትዳራቸው የፈረሰ፣ ንብረታቸውን ያጡ ግለሰቦች እንዳሉም የፖሊስ መረጃ ይጠቁማል፡፡
አዲስ አበባ ቤቴል የተባለው ሰፈር ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አለሚቱ ጉቱ በትዕግስት በደል እንደደረሰባት ቃሏን ለፖሊስ ሰጥታለች፡፡ ቤተሰቧቿ ወደ አምቦ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጉደር ከተማ የወሰዷት፣ ወ/ሮ ትዕግስት በበል ከህመምሽ ትፈውስሻለች በሚል እንደሆነ የተናገረችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ከተጠመቀች በኋላ ከቲቢ ካንሰር ተፈውሰሻል ብለው ህዝብ ተሰብስቦ በቪዲዮ እንደተቀረች ለፖሊስ ገልጻለች፡፡
ከዚህ በኋላ ደግሞ ልጆቼንና ወርቄን ነጥቃኛለች የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ልጆችሽ የእኔ እንጂ ያንቺ አይደሉም መባሏን ትናገራለች፡፡ ..አንድ ቀን የትንሿን ልጄን ጉር ሳበጥር ለምን ነካሻት ተብዬ እስከምዝለፈለፍ ድረስ ተደብዳቤአለሁ.. ትላለች፡፡
ከእኔ የትም አታመልጡም ስለምትል ሁሉም ይፈራታል የምትለው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ተከታዮቿ ..እመቤታችን ናት አምልኳት.. እንደሚሉ ትናገራለች፡፡ ..በምስል ታመልካላችሁ፤ ይኸው በአካል መጥታለች አምልኳት.. ይሉናል ብላለች፡፡ በየቀኑ ፆም አለ፤ በቀን አንዴ ንፍሮ እንበላለን ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ፆሙ የአዋቂ ብቻ ሳይሆን ከስድስት ወር ጀምሮ ያለ ህፃንም እንዲፆም ይደረጋል - ለሦስት ቀን ጡት አይሰጠውም ብላለች፡፡
ወ/ሮ ትዕግስት ትምህርት ሃጢያት ነው በሚል አቋም ልጆች እንዳይማሩ እንደምታደርግ አለሚቱ ለፖሊስ ተናግራለች፡፡
የ12 ዓመት ልጄን ከዚህ እንግልት ለማዳን እንጥፋ ብዬው ነበር፤ እሱ ግን ፈርቶ እምቢ አለኝ የምተለው - አለሚቱ፤ የባሰው መከራ የመጣው ግን የ3 ዓመት ልጄ ለ3 ቀን ያለ እህል ውሃ ፆም ፀሎት መያዝ አለበት ስትላት እንደሆነ ተናግራለች፡፡ ትልቁ ልጄ አሻፈረኝ ስላለ ሌላ ሙከራ ባደርግ ይገድሉኛል ብዬ ትንሿን ልጇን ይዛ እንደጠፋች ተናግራለች፡፡ የወንድ ልጇ ነገር ያላስቻላት ወ/ሮ አለሚቱ፤ ተመልሳ ወደ አምቦ መሄዷን ትናገራለች፡፡
ሆኖም ሰው ሁሉ ስለጠላቸው ወደ አዲስ አበባ ሄደዋል ተብላ መመለሷንና ልጇን ከቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማግኘቷን ገልጻ ለሳምንት ያህል አብሯት ከቆየ በኋላ እንደጠፋ ገልጻለች፡፡ ፖሊስ ልጇን ለሁለተኛ ጊዜ አግኝቶ የሰጣት ቢሆንም ተስማምተው ሊኖሩ እንዳልቻሉ እናት ትናገራለች፡፡ እኔን እንደ እናቱ ሳይሆን እንደ ጠላት ነው የሚያየኝ ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ..ማርያምን ከሰሻት እኔ ካንቺ ጋር አልኖርም.. ይላት እንደነበር ገልጻለች፡፡ ልጄ ..እኛ ምድራዊ አይደለንም፤ ሰማያዊ ነን.. እያለ እሷ የምትናገረውን ሲደግም ነገሩ ከአቅሜ በላይ እንደሆነ ስለገባኝ ወደ እነሱ እንዳይመለስ በማረሚያ ቤት እንዲቆይ ተደርጓል የምትለው እናቱ፤ አሁን ትንሽ ቢሻሻልም፤ እሷን ግን እንደጠላት እንደሚመለከታት ትናገራለች፡፡ ልጄ ጤነኛ አይደለም ያለችው ወ/ሮ አለሚቱ፤ ንብረቴን በሙሉ አጥቼአለሁ ከምንም በላይ የሚጽተኝ ግን ልጄን ማጣቴ ነው ብላለች - እንባዋን እያፈሰሰች፡፡ ወ/ሮ ትዕግስት አበራ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በእስር ላይ ስትሆን ጉዳይዋ ወደ ፍርድ ቤት ተልኮ በጊዜ ቀጠሮ ላይ እንደሆነ ታውቋል፡፡ወ/ሮ ትዕግስት ለፖሊስ በሰጠችው ቃል ..የሥላሴ መልዕክተኛ ነኝ እኔ ከወንድ ጋር አልተኛሁም፤ ተርፌሳም ማርያም ዮሴፍን ይጠብቃት እንደነበር ጠባቂዬ ነው፤ ሦስት ልጆች ቢኖሩኝም በመንፈስ ነው የወለድኳቸው፤ ይህንን ሁሉ ያደረኩት ሥላሴዎች አዘውኝ ነው፤ አላጠፋሁም.. ብላለች፡፡
ምንጭ አዲስ አድማስ http://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_content&view=article&id=790%3A2011-08-13-09-13-55&catid=76%3Ahot-topic&Itemid=994 በተጨማሪ ፖስት ያደረግነውን ቪዲዮ ይመላከቱ See part 1 http://dekikenabute.blogspot.com/2011/08/blog-post_7994.html?spref=fb part 2 http://www.facebook.com/video/video.php?v=137399669685908&comments&notif_t=video_commen    
part 3 http://www.facebook.com/video/video.php?v=137814382977770&comments&ref=notif&notif_t=video_comment 

Tuesday, August 23, 2011

መለየትን የሚወድ ምኞቱን ይከተላል. ምሳሌ ም .18 ቁ. 1


መለየትን የሚወድ ምኞቱን ይከተላል..
ምሳ ም 18 ቁ 1
"የሞት አያት ማነው?" ብለው በአንድ ወቅት መምህራችን ጠየቁን ሁሉም ለመመለስ አጁን አወጣ፡፡ በጣም ተደነኩ አኔ ግን "ደሞ ለሞትም የዘር ሀረግ አለው እንዴ ?"ብዬ መልሱን ለመስማት ቸኮልኩ፡፡ ብዙዎቻችሁ መልሱን እንደምታውቁት እገምታለሁ፡፡ ግን መልሱን ከማወቃችሁ በፊት ለዚህ ጥያቄ ምን አይነት ምላሽ ትገምቱ ይሆን? አኔ መልሱ እስኪመለስ ባለው ጊዜ በጣም ብዙ ነገር አሰብኩ፡፡ አኔ ካሰብኩት አንዱም መልስ አልነበረም፡፡
በሐዋርያው በቅዱስ ያዕቆብ መልእክት ምዕ 1 ቁ 12-15
"በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።  ማንም ሲፈተን። በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል፤ እግዚአብሔር በክፉ አይፈተንምና፤ እርሱ ራሱስ ማንንም አይፈትንም ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል።  ከዚህ በኋላ ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች፤ ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች።"
ንግዲህ የሞት አያቱ ምኞት ነው ማለት፡፡ መጽሐፍት አንደሚነግሩን
ዘፍ ም 3 ቁ 3-6"… እባብም ለሴቲቱ አላት። ሞትን አትሞቱም፤ ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።
ሔዋን ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ አየች(ተመኘች) ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ወለደች ማለትም ሔዋን ቆርጣ በላች (ሕገ እግዚአብሔርን አፈረሰች) የኃጢአት ደሞዙ (ልጅ) ሞት ነውና ሞት ተፈረደብን፡፡ ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በሞቱ ሞትን ሽሮልናል፡፡
አሁን በዚህ ዘመን ምኞታቸውን በመከተል መለያየትን በቤተክርስቲያናችን ለመፍጠር የሚጥሩ አንድና ሁለት አይደሉም፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን እንዳለ የራሳቸውን ክብር አንጂ የቤተክርስቲያን ጉዳይ ምናቸውም ያልሆነ በአጠቃላይ ምኞታቸውን ብቻ የሚከተሉ አባቶችን ከራሳቸው አሳንሰው ራሳቸውን ከፍ አድርገው የቤተክርስቲያን ልጆች እኛ ብቻ ነን የሚሉ (------እኔን ወለደች እገሌን ወለደች -------) ናቸው፡፡ "በልቡ ያለውን ሁሉ መግለጥ ብቻ ይወድዳል እንጂ" ምሳ ም 18 ቁ 2
አነዚህ ሰዎች በጣም የሚገርም ነገራቸው "ለካ ትወዱናላችሁ ለካ ታከብሩናላችሁ ለካ እኛ ብንወድቅ ይህ ሁሉ ሕዝብ ይወድቃል" እያሉ ህዝቡን በምላሳቸው በቃ ምን አለፋችሁ ሁሉም ነገር ምላሳቸው ላይ ነው ያለው፡፡ የቤተክርስቲያንን ፍቅር፤ የሕዝብ ፍቅር ----ወዘተ በምላሳቸው ምላስ ብቻ፡፡ ግን በተጨማሪ ምላሳቸው ከዚህ የተለየም ነገር አለው፤ ስድብ ፡፡ አትሳደቡ ብለው ግን አስተምረውን ያውቃሉ፡፡ ደሞ የት እንደሚሳደቡ ታውቃላቸሁ አውደ ምሕረት ላይ ቆመው፡፡ ምሳሌ (የንፍሮ ቀቃይ ልጅ፣ ……………………..) ከዚህም በላይ እኔ በጣም በእውነት እላችኋለሁ በጣም አዝናለሁ በአውደ ምሕረት ላይ "የጥፋት ርኩሰት ቆሞ ስታዩ ያኔ ሰሚው ያስተውል" 
አነዚህ ሰዎች እውነት አውደ ምሕረት ላይ ራሳቸውን ሳያርሙ፤ የሰደቡትን ሕዝብ ይቅርታ ሳይጠይቁ፤ ሳይማሩ(መቼም ምሥጢራተ ቤተክርስቲያንን ሳያውቁ እንደ ሚያውቁ ሆነው ሲያስተምሩ ሰምተናል ብዬ ነው) ማስተማር አለባቸው ትላላችሁ????
                                                የገዛ ምኞታችንን ከመከተል
የአግዚአብሔርን መልካም ፈቃድ እንድናውቅ
              ፈቃዱንም እንድንተገብር አግዚአብሔር ይርዳን!
የቅዱሳን አባቶቻችን ጸጋ በረከታቸው
ጥርጥር የሌለባት ሃይማኖታቸው
ድል የማትነሳ እምነታቸው
ከአኛ ከሁላችን ጋር ትሁን አሜን!!!!!!!!!

Friday, August 19, 2011

ይቅርታና ይቅር ባይነት

ይቅርታ ወይም ይቅር ባይነት የሰው ልጅ በዚህ ዓለም በሚኖርበት ወቅት በተለያዩ ማኅበራዊ ትስስሮች ወይም ግንኙነቶች አማካኝነት ከሌሎች የማኅበረሰቡ  ክፍሎች ጋር ለሚኖረው ጤናማ የኑሮ ጥምረት ትልቅ ድርሻ አለው ብዬ አምናለሁ። ይቅር መባባል ያለፈ በደልን አጥቦና አስወግዶ ለቀሪው ህይወት አዲስ ልቡናን በመፍጠር ግንኙነታችንን ወደ ተሻለ የኑሮ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል። በአንድ ወቅት በታሪክ አጋጣሚ ተበዳድለው፣ ተቀያይመው፣ ተኮራርፈው ከዚያም ባለፈ ደም ተቃብተው እና ለቂም በቀል ሌት ተቀን በሃሳብም በግብርም ይሯሯጡ የነበሩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በልቡናቸው የተቋጠረውን የመጠፋፋት ሕልምና ዕቅድ ወደ ጎን ትተው  አንዱ ካንዱ በጋብቻ እስከመጣመርና አንዱ ላንዱ ዋስ ጠበቃ እስከመሆን ያደርሳቸዋል። በዚሁ መልካም አጋጣሚ ምክንያትም ሊጠፋ የነበረው ሕይወት፣ ሊፈስ የነበረው ደም እና ሊጎድል የነበረው አካል ከጥፋት፣ ከመፍሰስና ከመጉደል ይድናል።


ከዚህም ባለፈ ቂም በቀል በይቅርታ እስካልተደመደመ ድረስ ጥፋቱ መቋጫ የለውም። አንዱ ላለፈ በደሉ አዲስ በደል ሲፈፅም ሌላኛውም አፀፋውን ሲመልስ የሁለቱም ወገኖች በምድር ላይ በሕይወት እስካሉ ድረስ መጠፋፋቱ ይቀጥላል። እንዲህ ዓይነቱ ለይቅርታ ቦታ አለመስጠት በተለይ ከሌላው ዓለም በተለየ መልኩ በእኛ በኢትዮጵያውያን ይብሳል። ምክንያቱ ምን ይሆን? በምጣኔ ሃብት አለማደጋችን፣ በቴክኖሎጂ አለመበልፀጋችን ወይም ገና ያልደረስንበትና ያልተማርነው ዘመናዊ ትምህርት ይኖር ይሆን? ትልቁ መንስዔ ከእነዚህ ምክንያቶች መካከል እንዳልሆነ የምንገነዘበው እነዚህ ምክንያትች ሞልተው የተትረፈረፉላቸው ወገኖቻችን ይባስ ብለው የችግሩ ሰለባ እነሱ መሆናቸው ነው።

ያደግንበት ማኅበረሰብም ሲወርድ ሲዋረድ በመጣው በእትንኩኝ ባይነትና ክንዴን ሳልንተራስ እንዴት እደፈራለሁ? አስተሳሰቡ በደንብ አድርጎ አጥምቆናል። ገና ከእናታችን ማኅፀን ከመውጣታችንም ደም መላሽ ብሎ ስም ያወጣልናል። አንደበታችን እማማ አባባ ማለት ሳይጀምር በቂም በቀል ዲፕሎማ ከቤተሰባችን እና ከአካባቢያችን በከፍተኛ ማዕረግ እንመረቃለን። ከዚያ በኋላ ልክ ግብፃውያን እናቶች ልጆቻቸውን አባይ ሕይወትህ ነው እያሉ እንደሚያሳድጉት ሁሉ ለእኛም የስማችንን ትርጓሜ ከወደፊቱ ስራችን ዕቅድ ጋር እየተነገረን እናድጋለን። ከዚህም በተጨማሪ ሕዝብን እናዝናናበታለን በሚል ሽፋን የሚወጡ ዘፈኖችም የራሳቸው ተፅዕኖ አላቸው። የአንድን ግለሰብ አስተሳሰብ ለመግለፅ እንዲሁም ለግጥሙ ቤት መድፋት እንጂ ጭብጡ በማኅረሰቡ ላይ የሚያመጣውን አሉታዊ ተፅዕኖ ባለማስተዋል የሚዘፈኑ ዘፈኖች አሉ። “ተበድዬስ ይቅርታ አልልም የቀረው ይቅር እንጂ” የሚል ዘፈን ሲያዳምጥና አብሮ ሲያንጎራጉር ያደገ ሰው ለይቅርታ ያለው ቦታ ቢያንስ ኸረ እስከ ጭራሹም ባይኖረው ምን ይደንቃል?

ሁላችንም እንደምናስታውሰው በጀግኖች አባቶቻችን ቆራጥ ተጋዳይነት ለጥቁር ሕዝብ ሁሉ የሚተርፍ የነፃነት ፋና በዓድዋ ተራሮች ተንቦግቡጎ ባልጠበቀውና ባላሰበው መልኩ ድል የተደረገው የኢጣልያ መንግስት ይህንን በዓለም አቀፍ አደባባይ የውርደት ሸማ ያለበሰውን የኢትዮጵያውያን ተጋድሎ ቂም ለመወጣት በተጠቀመው የመርዝ ጋዝ እጅግ ብዙ ወገኖቻችን በመሪር ስቃይ አልፈዋል። እስቲ እነዚህን የነፃነታችን አምድና ለዛሬው እኛነታችን የሕይወትን መስዋዕትነት ከፍለው ስማቸውን በልባችን ፅላት ላይ በወርቅ ማኅተም ያተሙትን ወገኖቻችንን አንድ ጊዜ ቆም ብለን እናስባቸው። 

በዚያን ጊዜ እነደዚያ ያለውን የጭካኔ ርምጃ እንዲወሰድ ያዘዘውን አካል ብናገኘውና እጅና እግሩ ታስሮ ፊት ለፊታችን ቢቀርብልን ምን ዓይነት ርምጃ ይሆን የምንወስድበት? እንደው የትኛውን የቅጣት ዓይነት ብንቀጣው ነው አንጀታችን ቅቤ የሚጠጣው? ምን ዓይነት የአገዳደል ስልት ብንጠቀምና ብንገድለው ነው  ያለፈውን የወገኖቻችን ሕይወት፣ የጎደለውን አካላቸውን እና የፈሰሰውን ደማቸውን ዳግም ማግኘት የምንችለው? ቁርጥርጥ አድርገን ብንፈጨውና ወደ አፈር ብንቀይረው ከዚያም ዳግም እንደ ጭቃ አብኩተን ሰውዬውን ሰርተነው እና ሃይሉ ኖሮን እስትንፋስ እንዲኖረው አድርገን እንደገና ብንቆራርጠው ይህንንም ሂደት ሕይወታቸውን ባጡት ወገኖቻችን ቁጥር ብንደጋግመው ስንቶቹን ይሆን ዳግም በሕይወት የምናገኛቸው? ምንም። እርሱ በከፈተው የክፋትና የጭካኔ ጎዳና አብረነው እንድንጓዝ እና እርሱ ለሰራው ጥፋት በሚጠየቅበት ቦታ ብቸኝነት እንዳይሰማው ከማድረግና ከሚከፈለው ክፍያ ተቋዳሽ ከመሆን ያለፈ ጠቀሜታ የለውም።

ታድያ ቂም በቀሉ ፋይዳው ምንድነው? የመንፈስ እርካታ ይገኝበት ይሆን? በቂም በቀል ደስታና እፎይታን ብሎም እርካታን የሚያገኘው መንፈስ እንዴት ያለው መንፈስ ነው? በእውነት ነፍሳችን በእንደዚህ ያለ ድርጊት ደስታን ታገኝ ይሆን? በጭራሽ። ቂም በቀል ጊዜያዊ የሆነ እርካታን ለስጋችን ይሰጠው ይሆናል እርሱም ቢሆን ቀን አልፎ ቀን ሲተካ ይፀፀታል። ያጣሁትን መልሼ ላላገኝ ይህንን ማድረጌ ምን ጠቀመኝ? ለምንስ የሰነፎችን መንገድ ተከተልኩኝ? እያለ ራሱን መውቀሱ አይቀሬ ነው።  በደልን በበደል፣ ክፋትንም በክፋት፣ ተንኮልንም በተንኮል እንሸፍናለን በሚል የዋህ አስተሳሰብ ታስረን የነገሮችን ውል ከማጥፋት ይልቅ ጥፋትን ተራርሞ ክፍተትን በይቅረታ መሙለቱ የታላቅነትና የአስተዋይነት ብሩሕ ምልክት ነው። ይህ ይቅርታና ይቅር ባይነት መገኛው የት ይሆን?

እንደ እኔ አመለካከት ይቅርታ እና ይቅር ባይነት ምንጩ መንፈሳዊ ሕይወት ነው። ምንም እንኳን ይቅርታ መደራረግ ለስጋዊ ኑሯችንም ታላቅ ጠቀሜታ ቢኖረውም ዋናውና ከዚህ የሚበልጠው ግን መንፈሳዊው ዋጋ ነው። ይህንን መንፈሳዊ ዋጋ ያገኝ ዘንድ ዘወትር የሚተጋ ሰው ልቡናው ለይቅርታ የፈጠነ ነው። በዚህ ምድር በበዳዩ ከተበደለው በደል ይልቅ በሰማይ የሚያገኘው ክብር ሚዛን ይደፋለታል። እዚህ ላይ ግን ሁላችንም ልንገነዘበው የሚገባን ነገር አለ። ይቅር ባይነት ቀላል አይደለም እንደማንኛውም ክብርን እንደሚያጎናፅፍ ተጋድሎ ሁሉ እርሱም ከፍተኛ ተጋድሎ ያሻዋል። በአፋችን ለመናገር እንደሚቀለው ያህል ለመተግበሩ ቀላል አይደለም። ይቅር ለማለት ስናስብ ብዙ ፈተናዎች ፊታችን ይጋረጣሉ። ፈተናው ከራስ ይጀምራል የቤተሰብ ፈተናም አለው እንዲሁም የአካባቢ ተፅዕኖም አለው። እነዚህን ፈተናዎች በድል አድራጊነት መወጣት የሚችል ሰው ነው ይቅር የሚለው እና ሰማያዊውን ክብር ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚያገኘው።

ቁርሾን በሆድ ይዞ ዘወትር መበላላትን፣ መጠፋፋትን እና ልኩን/ለኳን አሳያታለሁ ባይነትን የዘወትር መገለጫው የሆነውን ሰጋችንን ሰማያዊውን ተስፋ አሻግራ ለምትመለከተው ነፍሳችን ስናስገዛ መንፈሳዊነት በሕይወታችን በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደተለኮሰ ሻማ ከሩቅ ያበራል። የዚያን ጊዜ የበደሉንን አካላት መጥተው ይቅርታ እስኪሉን ሳንጠብቅ አስቀድመን ይቅርታን እናደርግላቸዋለን። የሰማያዊው ክብር ባለቤቶች መሆናችንን እናውቃለንና ይቅርታውን ባደረግን ወቅት ከመቼውም ይበልጥ ውስጣችን በሐሴት ይሞላል። የሰላም እንቅልፍም እንተኛለን።

ቸር ያሰማን፤ አሜን።

Thursday, August 18, 2011

በዚህ ዘመን ቅድስት ድንግል ማርያም በስጋ ተገለጠች ቢባሉ ምን ይላሉ?

አይን የማያየው የለም ጆሮም የማይሰማው የለም
በዚህችው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የዋሓንን አማኝ በማሳት በማታለል የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ እና ስርአት ለማጥፋት የሚጥሩ ብዙ የዋህ እንዳሉ የማይካድ እውነታ ነው ይህቺ ቤተ ክርስቲያን ከውጪ ያለችበት ከፍተኛ ፈተና ከፊት ተጋርጦ ሳለ እዚሁ በየገዳማቱ በየአድባራቱ ያሉትን የዋሀንን በፈለጉት ሀሳብ በመስበክ ሕዝቡን እያሳቱ እንዳለ ይህ እውነተኛ ምስክር ነው
  •        ማርያም በዚህ ዘመን ጌታን ለመውለድ ተገለጠች ቢባሉ ምን ይላሉ?
  •          እንደ አይሁድ ገና ጌታ ይወለዳል ቢባሉስ? 
  •      መለኮት ግንቦት 1/1999 ተፀንሶአል ይህንንም በ3 ቀን ሱባኤ ጠይቁ ቢባሉስ?
·         አረ ምኑ ቅጡ ሁሉንም ያድምጡት
በዚህ አይነት መልኩ ደጋፊ ማፍራት ይቻላል? 
see part 2 ተጨማሪ ከፌስ ቡካችን ያድምጡ ይህንም ይጫኑ
see part 3  ተጨማሪ ከፌስ ቡካችን ያድምጡ ይህንም ይጫኑ

ደቂቀ ናቡቴ

አክዓብም ናቡቴ በቤቴ አቅራቢያ ነውና የአትክልት ቦታ አደርገው ዘንድ የወይን ቦታህን ስጠኝ፤ ስለ እርሱም ከእርሱ የተሻለ የወይን ቦታ እሰጥሃለሁ፤ ወይም ብትወድድ ግምቱን ገንዘብ እሰጥሃለሁ ብሎ ተናገረው ናቡቴም አክዓብን የአባቶቼን ርስት እሰጥህ ዘንድ እግዚአብሔር ያርቅልኝ አለው እስከ ሞሞትም በቃ ለርስቱ የናቡቴ ልጆችም ዛሬ እርስታችንን ተዋህዶን ለእነ አድሳት ባዮች አንሰጥም እስከ ደም ጠብታ እንከፍላለን ሲሉ ነው

አባ ሙሴ ጸሊም


አባ ሙሴ ጸሊም በትውልዱ ኢትዮጵያዊ ሲሆን አስቀድሞ በውንብድና ኑሮ ሕይወቱን ይገፋ ነበር፡፡ ሰዎች ከገድሉ የተነሳ ያደንቁታል፡፡እርሱ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበርና እርሱ በሥጋው ጠንካራ ፤ በሥራውም ኃይለኛ ነበር፡፡
አባ ሙሴ ጸሊምም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ፤ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ፡፡ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር ፡፡
አባ ሙሴ ጸሊም ኢትዮጵያዊ
በአስቄጥስ ገዳም ያሉ መነኮሳት እግዚአብሔርን ያውቁታል ፤ ያዩታልም እያሉ ሲነጋገሩ ሰዎችን ሰማቸው፡፡ ያንጊዜም ተነሳ ሰይፉንም ታጥቆ ወደአስቄጥስ ገዳም ሄደ ፤ በደረሰም ጊዜ አባ ኤስድሮስን አገኘው ፤ አባ ኤስድሮስም ፈራው ሙሴ ጸሊምም እውነተኛውን አምላክ ታሳውቁኝና ታስረዱኝ ዘንድ ወደ እናንተ መጣሁ አለው ፡፡ አባ ኤስድሮስም ወደአባ መቃርስ ወስዶ አገናኘው፡፡ እርሱም ተቀብሎ ሃይማኖትን አስተማረው እንዲህም አለው ታግሰህ የማስተምርህን ከጠበቅህ እግዚአብሔርን ታየዋለህ
የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ አመነኮሰው ከብዙዎች ገድለኞች ቅዱሳን ይልቅ ብዙ እና ጽኑዕ ገድልን መጋደል ጀመረ፡፡፡፡በኋላም በገዳመ አስቄጥስ የገዳሙ አበምኔት የነበረው የአባ ኤስድሮስ ደቀ መዝሙር ሆነ፡፡ በአባ መቃርዮስ ምክር ወደ ጴጥራ ሂዶ በተባሕትዎ መኖር ቀጠለ፡፡ ከገድሉ ብዛት የተነሳ አረጋውያን መነኮሳት በሚተኙ ጊዜ ቤቶቻቸውን በመዞር ውሃ መቅጃዎቹን ወስዶ ውሃ ሞልቶ በየቤታቸው ደጃፍ ያኖር ነበር፡፡ ውሃው ከእነርሱ ሩቅ ነበርና እንዲህም እያደረገ በመጋደል ለብዙ ዘመናት ኖረ ፡፡
አባ ሙሴ ጸሊም በበአቱ እያለ የፈቲው ፆር ያሠቃየው ነበር፡፡ ፈተናውን ተቋቁሞ በበአቱ መቀመጥ ስላልቻለ ወደ ገዳሙ አበምኔት ወደ አባ ኤስድሮስ ዘንድ ሄደና ‹በበኣቴ መቀመጥ አልቻልኩም› አለው፡፡ አባ ኤስድሮስም ወደ በኣቱ ተመልሶ በዚያው እንዲጸና መከረው፡፡ ሙሴ ግን ‹ፈጽሞ አልችልም› አለ፡፡ በዚህ ጊዜ አባ ኤስድሮስ ሙሴን ይዞት ከገዳሙ ቅጥር ውጭ አወጣው ከዚያም ወደ ምዕራብ አዞረውና ‹ተመልከት› አለው፡፡ በዚያ አቅጣጫ የአጋንንት መንጋ ለወረራ ሲዘጋጁና ሲንጫጩ አሳየው፡፡ ቀጥሎ ደግሞ ወደ ምሥራቅ እንዲመለከት አደረገውና እልፍ አእላፍ መላእክት ብርሃን ተጐናጽፈው አሳየው፡፡ ከዚያም ‹እነዚህ የብርሃን መላእክት ቅዱሳንን ለመርዳት ከእግዚአብሔር የሚላኩ ናቸው እነዚህ ርኩሳን አጋንንት ደግሞ ቅዱሳንን ለመፈተን የሚዘምቱ ናቸው፡፡ የብርሃን መላእክት ኃይል ከአጋንንት ኃይል ይበልጣሉና ጸንተህ ተጋደል› ሲል መከረው አባ ሙሴም ወደ በኣቱ ተመለሰ፡፡
አባ ሙሴ በገዳመ አስቄጥስ እያለ ከገዳማውያን አንዱ ጥፋት ሠራና ማኅበሩ ለፍርድ ተሰበሰበ፡፡ አባ ሙሴ ግን በጉባኤው ላይ አልነበረም፡፡ ስለዚህ ካህኑ ተልኰ ‹ና. ሁላችንም አንተን እየጠበቅን ነው› አለው፡፡ አባ ሙሴም በሚያፈስስ ከረጢት አሸዋ ሞልቶ ያንንም በጀርባው ተሸክሞ ከኋላው እያፈሰሰ ወደ ጉባኤው አመራ፡፡ ጉባኤተኞቹ ተገርመው ለምን እንደዚህ እንዳደረገ ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹የእኔ ኃጢአቶች በኋላየ እንደዚህ አሸዋ በዝተው ይፈሳሉ፤ ነገር ግን ላያቸው አልቻልኩም ዛሬ ግን በሌላው ላይ ለመፍረድ መጥቻለሁ፡፡› አላቸው፡፡ ይህን ሲሰሙ ዝም አሉ፡፡ ያን ወንድምም በይቅርታ አለፉት፡፡
በሌላ ጊዜ በገዳመ አስቄጥስ ያሉ መነኰሳት ተሰበሰቡና የአባ ሙሴን ትዕግሥት ለመፈተን ሲሉ “ይህ ጥቁር መነኩሴ ለምን እዚህ መጣ “ ብለው ተናገሩት፡፡ እርሱም ዝም አለ፡፡ ጉባኤው ሲበተን “አባ ክፉ ስንናገርህ ምንም ሐዘን አልተሰማህም ነበርን ?” ሲሉ ጠየቁት፡፡ “ተሰምቶኛል፣ ነገር ግን እንዳልናገረው አንደበቴን ተቆጣጠርኩት” አላቸው፡፡
በአንድ ወቅት በገዳመ አስቄጥስ ጾም ታወጀ፡፡ በዚያ ሳምንት አባ ሙሴን ለማየት ከግብጽ ወንድሞች መጡ፡፡ አባ ሙሴም በእንግድነት ተቀበላቸውና ምግብ ያበስልላቸው ጀመር፡፡ የእሳቱን ጢስ የተመለከቱ ጐረቤቶቹ “አባ ሙሴ ትእዛዝ አፍርሶ ምግብ ያበስላል” ብለው ለገዳሙ ሓላፊዎች ተናገሩ፡፡ ሓላፊዎቹም ‹አሁን ተውት ሲመጣ እኛው ራሳችን እናናግረዋለን› አሏቸው፡፡ ሓላፊዎቹም አባ ሙሴን ጠርተው ለምን ምግብን እንዳበሰለ ተረዱ፡፡ በቀዳሚት ሰንበት ማኅበሩ ሁሉ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጣ በአደባባይ ‹አባ ሙሴ ሆይ የሰውን ትእዛዝ አልጠበቅኽም፤ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ (እንግዳ ሆኜ መጥቼ ተቀብላችሁኛል የሚለውን) ግን ጠብቀሃል› ብለው አመሰገኑት፡፡
አንድ ጊዜ የአካባቢው ገዥ ስለ አባ ሙሴ ዝና ሰምቶ ያየው ዘንድ ወደ ገዳመ አስቄጥስ መጣ፡፡ ይህን የሰማው አባ ሙሴ ሸሽቶ ወደ ጫካ ገባ፡፡ በመንገድም ላይ የገዥው መልእክተኞች አገኙትና ‹እባክህ አባ ሙሴ የት እንዳለ በኣቱን አሳየን› አሉት፡፡ ‹ከርሱ ምን ትሻላችሁ፤ እርሱ ኮ ቂላቂል ነው› አላቸው፡፡ ይህን የሰማው የአካባቢው ገዥ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መጣና የሆነውን ሁሉ ለአገልጋዮች ነገራቸው፡፡ ‹ብዙ ሰዎች ስለ አባ ሙሴ ሲያወሩ ሰምቼ ለማግኘት መጥቼ ነበር፤ በመንገድ ላይ ያገኘነው አንድ አረጋዊ ሰው ግን የአባ ሙሴ በኣት የት እንደሆነ ስንጠይቀው ከርሱ ምን ትሻላችሁ እርሱ ኮ ቂላቂል ነው አለን› ብሎ ነገራቸው፡፡ አገልጋዮቹም በጣም ተናደዱና ‹ምን ዓይነት አረጋዊ ሰው ነው ስለ ቅዱሱ ይህን የሚናገር› ብለው ጠየቁት፡፡ ‹ትልቅ፣ ጠቆር ያለ፣ አሮጌ ልብስ የለበሰ ነው› አላቸው፡፡ አገልጋዮቹም ተገርመው ‹ይህማ ራሱ አባ ሙሴ ነው፤ ይህን ያለህ ሊያገኝህ ስላልፈለገ ነው› አሉት፡፡ የአካባቢው ገዥም ከአባ ሙሴ ሁኔታ ከንቱ ውዳሴን ስለ መሸሽ ትልቅ ትምህርት ተምሮ ተመለሰ፡፡
አባ ሙሴ በኣት ሠርቶ ወደ ጴጥራ ሲሄድ በአካባቢው ውኃ ስላልነበረ ተጨንቆ ነበር፡፡ አንድ ድምፅ ‹ሂድ ስለምንም ነገር አትጨነቅ› አለው፡፡ ስለዚህም በዚያ መኖር ጀመረ፡፡ አንድ ቀን በጴጥራ እያለ አበው ሊጐበኙት መጡ፡፡ የነበረችው ውኃ ጥቂት ነበረችና በርሷ ምግባቸውን አበሰለ፡፡ የሚያጠጣቸው ግን አላገኘም፡፡ ስለዚህ ወደ ውጭ እየወጣ ውኃ ይሰጠው ዘንድ እግዚአብሔርን ይለምን ነበር፡፡ በመጨረሻ ዝናብ ዘነበና የውኃ ማጠራቀሚያዎቹን ሁሉ ሞላቸው፡፡ እነዚያ አባቶችም ‹ትወጣና ትገባ የነበረው ለምን እንደሆነ እባክህ ንገረን› አሉት፡፡ ‹እናንተ በእንግድነት ስትመጡ ውኃ አልነበረኝም፣ ስለዚህ ያንተን አገልጋዮች ወደ እኔ ልከሃቸዋል፣ ነገር ግን ውኃ የለኝም፣ ስለዚህ እባክህ ውኃ ስጠኝ እያልኩ እግዚአብሔርን ለመለመን ነበር› አላቸው፡፡
አንድ ወንድም አባ ሙሴን ‹አንድን አገልጋይ ባጠፋው ጥፋት የተነሣ ጌታው መታው፡፡ አገልጋዩ ምን ማለት አለበት?› ብሎ ጠየቀው፡፡ አባ ሙሴም ‹አገልጋዩ ብፁዕ ከሆነ፣ አጥፍቻለሁና ይቅር በለኝ ማለት አለበት፡፡› አለው፡፡ ‹ሌላ አይጠበቅበትምን?› ሲል ያ ወንድም ጠየቀው፡፡ ‹አይጠበቅበትም፣ ለጊዜው ለጥፋቱ ሓላፊነቱን ወስዶ አጥፍቻለሁ ካለ ጌታው ይቅር ይለዋል፡፡ የዚህ ሁሉ ዓለማው በባልጀራ ላይ ላለመፍረድ ነው፡፡ በእውነቱ ጌታችን የግብጽን በኩራት ሁሉ ሲመታ ሰው ያልሞተበት አንድም ቤት አልነበረም› አለና መለሰለት፡፡ ያም ወንድም ‹ምን ማለት ነው?› አለው፡፡ ‹ሁላችንም የየራሳችንን ጥፋቶች ካየን የባልንጀራችንን ለማየት ዕድል አንሰጥም፡፡ በራሱ ቤት ሰው የሞተበት በጐረቤቱ ልቅሶ ለማልቀስ አይሄድም፡፡ ለባልንጀራ መሞት ማለት ለራስ ጥፋት ትኩረት በመስጠት፣ የሌላውን ጥፋት ከቁም ነገር አለመቁጠር ነው፡፡ ማንንም አትጉዳ፣ በማንም ላይ ክፉ አታስብ፣ ክፉ የሚሠራውን ሰው አትናቀው፣ በባልንጀራው ላይ ክፉ በሚሠራ ሰው ላይ አትተማመን፣ በባልንጀራው ላይ ክፉ ከሚሠራ ሰው ጋር አትደሰት፣ ለባልንጀራ መዋቲ መሆን ማለት ይህ ነው፡፡ በማንም ላይ አትማረር፣ ነገር ግን ‹ሁሉንም እግዚአብሔር ያውቃል፡፡› በል፡፡ ከሚያማ ሰው ጋር አትተባበር፣ በሐሜቱም አትደሰት፣ ወንድሙን የሚያማውን ሰውም አትጸየፈው፡፡ አትፍረድ ማለት ትርጉሙ ይህ ነው፡፡ በማንም ላይ የጥላቻ ሓሳብ አይኑርህ፣ ጥላቻ ልብህን እንዲያሸንፈውም አትፍቀድለት፡፡ ባልንጀራውን የሚጠላውን አትጥላው፣ ሰላም ማግኘት ማለት ይህ ነው፡፡
አንድ ጊዜ በገዳመ አስቄጥስ ወንድሞች አብረውት እያሉ አባ ሙሴ ‹ተመልከቱ በርበሮች ገዳማችንን ሊያጠፉ እየመጡ ነው፡፡ ተነሡና ሽሹ› አላቸው፡፡ እነርሱ ግን ‹አባ አንተስ አትሸሽምን?› ሲሉ ጠየቁት፡፡ አባ ሙሴም ‹እኔማ ይህችን ቀን ለብዙ ዘመናት ስጠብቃት ኖሬአለሁ፡፡ ጌታ በወንጌል ‹ሰይፍን የሚያነሡ በሰይፍ ይጠፋሉ› ያለው ቃል (ማቴ. 25.52) ይፈጸማል፡፡› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹እኛም አንሸሽም፣ አብረን እንሞታለን እንጂ› አሉት፡፡ አባ ሙሴም ‹ያ ለእኔ ረብ የለውም፤ ሁሉም ሰው ለየራሱ ይወስን› ብሉ መለሰላቸው፡፡ በዚያ ለነበሩት ሰባት ወንድሞች ‹በርበሮች ወደ ገዳሙ ደጅ እየደረሱ ነው› ብሎ ነገራቸው፡፡ ወዲያውም በርበሮቹ ደርሰው ገዳማውያኑን በሰይፍ መቷቸው፡፡ ከሰባቱ ደቀ መዛሙርት አንዱ ሸሸና በተቆለለው ሰሌን ውስጥ ተደበቀ፤ ወዲያውም ሰባት አክሊላት ሲወርዱላቸው ተመለከተ፡፡
የአባ ሙሴ ጸሊም በረከት ይደርብን አሜን
ዋቢ ስንክሳር ሠኔ 24
በበረሓው ጉያ ውስጥ

የተለያዩ ጊዜ በጋሻው የፈጸማቸው ስህተቶች


Friday, August 5, 2011

የዐሥርቱ ትዕዛዛት ዓላማ





ዐሥርቱ ትዕዛዛት የተሰጡት በሚከተሉት ዓላማዎች ነው፡፡ ይኸውም፡-

1. ከግብጽ ምድር ስላወጣቸው ውለታውን እንዲያስቡ
2. ወደ ፊት በአረማዊያን መካከል ሲመላለሱ ከኃጢአት እንዲቆጠቡ
3. መንፈሳዊ አካሄዳቸው ምን ምን አቅጣጫ መከተል እንዳለበት ለማሳየት ነው፡፡

የዐሥርቱ ትዕዛዛት አከፋፈል

የክርስቲያን ሕግ የፍቅር ሕግ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሌላውን የሚወድ ሕግን ፈጽሞበታል ካለ በኋላ ከዐሥርቱ ትዕዛዛት የተወሰኑትን በመጥቀስ ፍቅር የሕግ ሁሉ ፍጻሜ መሆኑን በግልጽ ይነግራል፡፡ ሮሜ 13፡8-10 ታዲያ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረ ፍቅር በሁለት ይከፈላል፡፡ ማቴ 22፡34-41

1 ፍቅረ እግዚአብሔር 2 ፍቅረ ቢጽ

1. ፍቅረ እግዚአብሔር ከአንደኛ ትዕዛዝ እስከ ሦስተኛው ያሉት ሲሆኑ እግዚአብሔርን የሚመለከቱ ናቸው፡፡

2. ፍቅረ ቢጽ ከአራተኛ ትዕዛዝ እስከ አሥረኛ ትዕዛዝ ያሉት ሲሆኑ በለእንጀራን የሚመለከቱ ናቸው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በአዎንታዊና በአሉታ ከመነገራቸው አንጻር በሁለት ይከፈላሉ ይኸውም፡-
1. ሕግ በአሉታ የተነገሩ /አታድርግ/
2. ትዕዛዝ በአዎንታ የተነገሩ /አድርግ/

ከዚህም ሌላ ከአፈጻጸማቸው አንጻር ሲታዩ በሦስት ይከፈላሉ፡፡

1. በሐልዮ የሚፈጸሙ 1፣3፣4 እና 9 በሐሳብ
2. በነቢብ የሚፈጸሙ 2፣ 8 በመናገር
3. በገቢር የሚፈጸሙ 5፣6፣7 እና 10 በሥራ ናቸው፡፡

ብሂለ አበው

0 ለተወሰን ጊዜ ለሀይማኖት መከራከር፤ጠበቃ መሆን፤መዋጋት ብሎም መሞት አይከፋም ሁልጊዜ ለሀይማኖት መኖር ግን ከሁሉ የበለጠ መስዋእትና ክብር ያለው ህይወት ነው፡፡

o የረብዑ ምግብ ለሀሙስ የአርብ ምግብ ለቅዳሜ ይጠቅማል ነገር ግን የማክሰኞ ምግብ ለረብዑ አይጠቅምም የሀሙስ ምግብ ለአርብ አይሆንም የነፍስና የስጋ ነገርም እንዲሁ ነው፡፡


o የነፍሳችን ነገር ትተን የስጋችንን ብቻ የምናደልብ ከሆነ ነፍስን በስጋ መቃብር እየቀበርናት መሆኑን አንርሳ

o አንድ በርሜል ወተት በአንድ ጠብታ ኮምጣጤ የበጣጠሳል የብዙ ጊዜ ተጋድሎንም ጠብታ የሀጢያት ኮምጣጤ ያበላሸዋል


o ራስህን በሀሰት አትውቀስ፡፡ራስህ መክሰስ ትህትና አይደለም፡፡ ታላቅ ትህትና ሰዎች ሲወቅሱህ መታገስ ነው

o ትዕቢት ሰይጣን ያለመው ጦር ነው

o ትህትና ህፀፅን የምታስታውቅ መስታወት ናት

o ክርስትና ማለት የሰውን ሸክም መሸከምና እስከሞት ድረስ መፅናት ማለት ነው

o በባልንጀራው ላይ ክፋትን የሚያስብ ሰው ያችው የሚያስባት ክፋት ራሱን ትጎዳዋለች፡፡ በየትና ምን ጊዜ እደምትጥለው ግን አያውቅም

o ስንፍናውን ወደጥበብ፤አላዋቂነቱን ወደእውቀት ፤መጥፎ ጠባዩን ወደበጎነት የሚመልስ ሰው ብርቱ ነው

o ፀሎት ገንዘብን ሊያመጣ ይችላል፡፡ ገንዘብ ግን ፀሎትን አያመጣም፡፡

ብሂለ አበዉ


• ‹‹እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ››
አባ እንጦንስ
• ‹‹ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻልን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻልናል››
ቅዱስ አትናቴዎስ
• ‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ ነደደ ይኖራል››
ቅዱስ ሚናስ
• ‹‹በማንም ላይ ክፈትን አትስሩ አትፍርዱ ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና››
ታላቁ አባ መቃርስ
• ‹‹ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናልሁ በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም››
ቅዱስ አርሳንዮስ
• ‹‹ቤተክርስትያን መጠጊያችን ነች ቤተክርስትያን የኖኅ መርክብ ነች በውስጧ እንጠለላልን ከውጭዋ ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል››
ቅዱስ እንድርያስ
• ‹‹ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከኾነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ከበደል በንስሐ ነጹሕ ካደረግነው በጸጋ መንፈስቅዱስ የተሞላን እንሆናለን››
አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን
• ‹‹ስጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ህይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው››
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
• ‹‹የቤተክርስቲያን ህይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ህይወታችሁ ይልቅ የቤተክርስቲያናችሁን አቋም አጠንክሩ››
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
• ‹‹ከመኝታህ በፊት የምታደርገውን ፀሎት ትተህ እንድትተኛ መንፈስህ ሲገፋፋህ እሺ ብለህ አትቀበለው፡፡ እንዲያውም መዝሙረ ዳዊትን ጨምርና ሌሊቱን በሙሉ ስትፀልይ እደር››
ቅዱስ ይስሀቅ ሶርያዊ
• ‹‹ኃጥያታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል ኃጥያታችንን እኛ እረስትን የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል››
ቅዱስ እንጦስ

አሰግድ ሣህሉ “ተሐድሶ ማለት እኔ ነኝ” አለ


* በስም ማጥፋት ወንጀል የተከሰሱት አባ ሰረቀ ከሀገር ሊወጡ ነው፤

(ደጀ ሰላም፤ ኦገስት 5/2011)፦ ወደ ቤተ ክርስቲያን የውስጥ መዋቅር በመግባት የፕሮቴስታንታዊ-ተሐድሶ-ኑፋቄን ዓላማ ለማሳካት ከሚፍጨረጨሩትና ከእነርሱም መካከል እንደ ዋነኛ ከሚታዩት የወቅቱ የአፅራረ ቤተ ክርስቲያን ቅጥረኞች አንዱ ሆነው አሰግድ ሣህሉ “ተሐድሶ ማለት እኔ ነኝ” ሲል በገዛ አንደበቱ መናገሩ ተሰማ፡፡ አሰግድ ይህን ምስክርነት ስለ ራሱ የሰጠው ከነገ በስቲያ ቅዳሜ ለንባብ እንደሚበቃ በተጠቆመ አንድ መጽሔት ሰሞኑን በሰጠው ቃለ ምልልስ ነው፤ ንግግሩንም በአንድ ወቅት በ‹ተሐድሶ› ጉዳይ ላይ ለጠየቀችው አንዲት ሴት የመለሰው መሆኑ ተገልጧል፡፡



ግለሰቡ ቃለ ምልልሱን ከሰጠና መጽሔቱ ዝግጅቱን አጠናቅቆ ወደ ማተሚያ ቤት ከገባ በኋላ ይህ ቃሉ ከቃለ ምልልሱ እንዲወጣለት አልያም ቃለ ምልልሱ ጨርሶ እንዲቀር “ደኅንነቶች ናቸው” በሚላቸው ግለሰቦች ዋና አዘጋጁን ማስፈራራቱ ታውቋል፡፡ አሰግድ በተለያዩ አጋጣሚዎች “ደኅንነቶች ናቸው” በሚላቸው ግለሰቦች እያስፈራራ ሕገ ወጥ ፍላጎቱን እንደሚያስፈጽም ያስታወሱት የዜና ምንጮቹ ግለሰቡ ከዚህ መንገዱ እንዲታቀብ ሊገደድ እንደሚገባው ያሳስባሉ፡፡







አሰግድ ባለበት የሃይማኖት ችግርና ባቀረበው የተጭበረበረ የትምህርት ማስረጃ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከትምህርት ገበታ ቢያገደውም ታኅሣሥ 27 ቀን 2003 ዓ.ም በኮሌጁ ላይ በመሠረተው ክስ “የኮሌጁ ውሳኔ አግባብ አይደለም” በሚል ሐምሌ ሰባት ቀን 2003 ዓ.ም ትምህርቱን እየተከታተለ እንዲቀጥል ፍርድ ቤቱ ውሳኔ መስጠቱ ተዘግቧል፡፡ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ጥር 27 ቀን 2003 ዓ.ም ለክሱ በሰጠው ምላሽ፣ “ጉዳዩ የሃይማኖት ክርክርን የያዘ ስለሆነ ፍ/ቤቱ አከራክሮ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን የለውም” ሲል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርቧል፡፡ የፍሬ ነገር ክርክሩንም በተመለከተ፣ “ከሳሽ ቤተ ክርስቲያን የማትቀበለውን ትምህርት የሚያራምዱ በመሆናቸው፣ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት በዚሁ ጉዳይ አቤቱታ ቀርቦባቸው ቤተ ክርስቲያንም ይህን ማረጋገጧ፣ ከሳሽ ያለሰበካቸው በማታለል የቀበና መድኃኔዓለም ሰበካ ጉባኤ አባል ነኝ በማለታቸው ያቀረቡት ማስረጃ በደብሩ አስተዳዳሪ የተሰረዘ በመሆኑ” የከሳሽ ክስ ውድቅ እንዲደረግ ጠይቆ ነበር፡፡ ደጀ ሰላም የጡመራ መድረክ በጉዳዩ ላይ ተከታታይ ዘገባዎችን (http://www.dejeselam.org/2011/02/blog-post_10.html) ማቅረቧ ይታወሳል፡፡



በሌላ በኩል በማኅበረ ቅዱሳን ላይ በየጊዜው በፈጸሙት የስም ማጥፋት ድርጊት ክስ ተመሥርቶባቸውና በማስረጃ ተመስክሮባቸው እንዲከላከሉ ትእዛዝ የተሰጣቸው የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ሓላፊ አባ ሰረቀ በአቡነ ጳውሎስ ጥያቄ ፍትሕ ሚኒስቴር ክሱ ለጊዜው እንዲቋረጥ ካስደረጉ በኋላ ነገ ቅዳሜ ወደ አሜሪካ ዋሽንግተን - ዲሲ ለመብረር መዘጋጀታቸው ተጠቁሟል፡፡ በዋና ሓላፊው ጥብቅ ቁጥጥር ሥር በሚዘጋጀው የመምሪያው ድረ ገጽ ላይ “ክሱ ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ በነጻ እንደተሰናበቱ” አስመስለው እንዲዘገብ ያደረጉት አባ ሰረቀ ከሕግ የበላይነት ለመሸሽ በጀመሩት መንገድ ከሀገር ለመውጣት መወሰናቸውን ነው ምንጮቹ የጠቆሙት፡፡ አባ ሰረቀ በድረ ገጹ ያወጡት የተሳሳተ ዘገባ እንዲታረም ክሱ ለጊዜው እንዲቋረጥ ባዘዘው በፍትሕ ሚኒስቴር ሰዎች ቢነገራቸውም “እምቢ፣ አይሆንም፣ አልሰርዘውም” አልኳቸው እያሉ በጀብድ መልክ ሲያወሩ መሰንብታቸው ተገልጧል፡፡ የ1200 ዜጎችን ከ56 ሚልዮን ብር በላይ አላግባብ ወስዷል የተባለው የአስካሉካን ትሬዲንጉ ግርማይ ከሕግ ተጠያቂነት መሸሽ እንደማይችል ታውቆ ሰሞኑን በኢንተርፖልና በመንግሥት ጥረት በቁጥጥር ሥር ውሎ ወደ ሀገር ቤት ተመልሷል፡፡ የእኛው አባ ሰረቀስ? የፍትሕ ፈላጊ ኦርቶዶክሳውያን ጥያቄ ነው፡፡

Friday, July 29, 2011

ቤተ ክህነቱ ያጣው የቤተ ክህነቱ ሰው


ሦስቱ ጠባየ ጳጳሳት

ቤተ ክህነቱ በየዘመናቱ ሦስት ዓይነት ጠባየ ጳጳሳትን አስተናግዷል፡፡ የመጀመሪያው እና የአብዛኛዎቹ የሆነው አድርባይነት ነው፡፡ የዚህ ምንጩ ደግሞ በዓላማ ለዓላማ የመላእክትን አስኬማ አለመድፋት ነው፡፡ የመላእክት አስኬማ /ምንኩስና/ ንጽሕናን ይጠይቃል፣ ብዙዎቹ ንጽሕናቸውን አጉድፈዋል፡፡ የመላእከት አስኬማ የዚህን ዓለም ጣዕም ይንቃል፤ ብዙዎቹ ዓለማዊነትን ኑሮ አድርገውታል፡፡ የመላእክት አስኬማ የራሴ የሚለው ዘውግ እና ንብረት የለውም፡፡ ብዙዎቹ ግን የዘውግ ብል የበላቸው፤ የዚህ ዓለም ሀብትና ንብረት ያማለላቸው ናቸው፡፡ ይኽ ደግሞ ጥብዓት የጎደላቸው፤ ትጋሀ ሌሊት የማያውቃቸው፣ የመንኖ ጥሪት መዓዛ የማይሸታቸው አድርባዮች እንዲሆኑ አድርጓቸዋል፡፡ በምስጢር የፈጸምናቸው ስህተቶች ከአሁን አሁን ተደረሶባቸው እንጋለጥ ይሆን በሚል የሚደነብሩ እና የማፍያው ቡድንም ይኽን የጎደፈ ገመናቸውን ለምእመኑ እገልጣለሁ እያለ የሚያስፈራራቸው እና ከፍርሃታቸውም የተነሣ ለዚህ ቡድን ፈቃድ እንዲያድሩ አድርጓቸዋል፡፡

ሁለተኛው እና ቁጥራቸው ቀላል ያልሆኑ ጳጳሳት ጠባይ ደግሞ ቸልተኝነት ነው፡፡ የእነዚዎቹ ቸልተኝነት ከጠባቂነታቸው እና ከስንፍናቸው የሚመጣ ነው፡፡ ምንም እንኳን የመላእክት አስኬማ መለያ የሆነው ቅድስና፣ ዘውግ አለመለየት፣ የዓለምን ፈቃድ ማሸነፍን ገንዘብ ቢያደርጉም የጠባቂነት እና የስንፍና ቅንቅን ወሯቸዋል፡፡ ለቤተክርስቲያን የሚሆነውን ሠርተው ከማለፍ ይልቅ ሌሎች እንዲሠሩ ይፈልጋሉ፡፡ እነርሱ መስዋዕት ከሚከፍሉ በሌሎች መስዋዕትነት የቤተክርስቲያንን ዕድገት ማየት ይፈልጋሉ፡፡ እነርሱ የጎደለውን ከሚያሟሉ፤ የጠመመውን ከሚያቀኑ ሌሎች በሚያሟሉት እና በሚያቀኑት ፍኖት መጓዝን ይመርጣሉ፡፡ እነርሱ ተናግረው ከሚያሳምኑ ይልቅ ሌሎች ተናግረው እንዲያሳምኑላቸው ይፈልጋሉ፡፡ እነርሱ ታሪክ ሠርተው ከማለፍ ይልቅ የተሠሩ ታሪኮችን እያመነዠጉ የታሪክ ግብ ይቅርና ምዕራፍ ሳይኖራቸው ያለፉ፤ የሚያልፉ ሰነፎች ናቸው፡፡ እነርሱ የተጣለባቸውን ሓላፊነት በቆራጥነት ከመወጣት ይልቅ ቅዱስ ፓትርያርኩ «ከተስማሙበት ምን አገባን» የሚሉ፤ ቤተክርስቲያን በሰላም ማጣት፣ በመናፍቃን ሴራ፣ በመልካም አስተዳደር ዕጦት ስትታመስ እየተመለከቱ እነዚህ ሁሉ ችግሮች በአንድ ጀንበር በፓትርያርኩ ሞት የሚፈታ ይመስል ሞት ናፋቂዎች ሆነዋል፡፡ ይኽ መሆኑ ደግሞ ቤተክህነቱን ብቻ ሳይሆን ቤተ ክርስቲያኒቱን በበላተኞች እንድትወረር፣ ቅሰጣ እንዲደረግባት የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡

ሦስተኛው ጠባየ ጳጳሳት እና በቤተክህነቱ በጥቂቱም ቢሆን ትላንት የነበረ፤ ዛሬ ግን ያጣው ጴጥሮሳዊነት ነው፡፡ ጴጥሮሳዊነት ሰማዕተ ጽድቅ ዘኢትዮጵያ በሆኑት በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕትነት ላይ የቆመ ነው፡፡ ይኽ ደግሞ ስለ እውነት በእውነት መሞት ልዩ ግብሩ ነው፡፡ ጴጥሮሳዊነት ከላይ እንደተመለከትነው ሁለቱ ጠባየ ጳጳሳት ሳይሆን በእግዚአብሔር አምኖ የራስንም ሓላፊነት እየተወጡ ውጤቱን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ብሎ መቀበል ነው፡፡ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም «ኢትዮጵያ ከየት ወዴት)» በሚለው መጽሐፋቸው ስለ ጴጥሮሳዊነት እንዲህ ብለዋል፡፡

«. . .ጴጥሮሳዊነት በመሠረቱ መንፈሳዊነት በመሆኑ የሚመካበትም ኀይል መንፈሳዊ እንጂ አካላዊ ወይም ጠመንጃ አይደለም፡፡ የጴጥሮሳዊነት ዓላማ አስፈላጊ ከሆነ ለእምነቱ፣ ለሀገሩና ለወገኑ ለመሞት እንጂ ለመግደል አይደለም፡፡. . . ለመሞት መዘጋጀትና ለእውነትና ለእምነት መሞት ግን ወኔን ይጠይቃል፡፡ መንፈሳዊ [ጴጥሮሳዊ]ወኔ፡፡» /ገጽ.44/

ሦስቱ የጴጥሮሳዊነት ምንጭ

ጴጥሮሳዊነት በመንፈሳዊነት ላይ የቆመ የመላእክት አስኬማ ነጸብራቅ እንደመሆኑ ከሦስት ነገሮች ይመነጫል፡፡

1 አደራን ለመጠበቅ ዝግጁ ከመሆን

አደራ ክቡር፣ ውድ፣ ታላቅ ምስጢር ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙሩ የሆነው ጢሞቴዎስን የተሰጠውን አደራ በመጠበቅ ሓላፊነቱንና ግዴታውን መወጣት እንደ ሚገባው ሲገልጽ «እቀብ ማህጸንተከ፤ አደራህን ጠብቅ» በማለት ነው፡፡ 1ኛጢሞ.6 .2፡፡ ጢሞቴዎስ በመምህሩ የተጣለበትን አደራ ለመወጣት የዚህ ዓለም ፈቃድ ሳያሸንፈው ተወጥቷል፡፡ የዓላውያን ነገሥታት ማዋከብ፣ ድብደባ አደራውን እንዳይወጣ አላደረገውም፡፡ የአቡነ ጴጥሮስ የሰማዕትነትም ጉዞ መነሻውም መድረሻውም የእነዚህ አባቶች አርአያ ፍኖት ነው፡፡

ለሀገራቸውና ለወገናቸው እስከ መጨረሻዋ ሰዓት ድረስ እውነቱን ከሐሰት በመለየት ለሕዝባቸው የሰጡት ምስክርነት የተጣለባቸውን አደራ ከመወጣት ነው፡፡ አለቃ ተጠምቀ የተባሉ ቅድስናን ከሊቅነት ጋራ አስተባብረው የያዙ የቅኔ መምህራቸው አንድ ቀን ብፁዕነታቸውን ጠርተው የሚከተለውን የአደራ ቃል ያስተላልፋሉ፡፡ «ኀይለማርያም አንተ ወደፊት ጳጳስ ትሆናለህ፤ በወቅቱም አረመኔ በዚህች ሀገር ይሠለጥናል፡፡ ታዲያ ያኔ አንተ ለነፍስህ ሳትሳቀቅ በሰማዕትነት እለፍ፤ ሰማዕትነት ክፍልህ ነው፡፡ አደራ፡፡» /መርሻ አለኸኝ /ዲያቆን/፣ 1986 ዓ.ም፣ ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን፣ ገጽ.80/

ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስ የመምህሩን የአደራ ቃል በመያዝ እስከ መጨረሻው እንደጸናው ብፁዕነታቸውም የመምህራቸውን የአደራ ቃል በሰማዕትነት አትመው ጠበቁ፡፡ አንዲትም ቀንና ሰዓት ከሞት ሳይሸሹ እና ሳይደበቁ ለአገራቸው ፣ለቤተ ክርስቲያናቸው እና ለሕዝባቸው ሲሉ ሞትን ተጋፈጡ፡፡ የሰማዕትነትን ጽዋ ተጎነጩ፡፡ የዚህ ምንጩ አደራ ነው፡፡ እኔም የጴጥሮሳዊነት አንዱ ምንጩ አደራን ለመጠበቅ ዝግጁ ከመሆን ይመነጫል የምለው ለዚህ ነው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቤተክርስቲያን በአደራ የሰጠቻቸውን ሓላፊነት ለመወጣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በጸሎታቸው እየደገፉ፣ በትምህርታቸው እያበረቱ አስተዳድረዋል፡፡

የጴጥሮስን ሥልጣን የያዙ፣ አስኬማውን የደፉ፣ ካባውን የደረቡ፣ መስቀሉን ከእነ በትረ ሙሴው የጨበጡት «ዘመነኞቹ» ጳጳሳት ከቤተክርስቲያን የተቀበሉትን የእረኝነት የአደራ ቃል በመተው ለቤተክርስቲያን ከሚታገሉላት ይልቅ የሚታገሏት ሆነዋል፡፡ ጵጵስናውን ሲቀበሉ የገቡትን ቃለ አደራ በመዘንጋት በጴጥሮሳዊነት ለአገርና ለወገን ሊቆሙ ይቅርና ክብርን ለአጎናጸፈቻቸው እናት ቤተክርስቲያን የማይሆኑ እርባና ቢስ ሆነዋል፡፡ ፍርሃት ድሩን ሠርቶባቸው ትምእርተ ምንኩስናቸውን ሸፍኖታል፡፡ ሹመታቸው የዖዝያን ሹመት እስኪመስል ድረስ የጽድቅ ፈሪዎች፤ የኃጢአት ደፋሮች አስመስሏቸዋል፡፡

2. አባታዊ ሓላፊነትን ከመወጣት

የሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕትነት አባታዊ ሓላፊነታቸውን በቆራጥነት ለመወጣት ካደረጉት ተጋድሎ ይመነጫል፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሕዝብ ቀስቅሰዋል፤ ራስዎም አምጸዋል፣ ሌሎችንም እንዲያምጹ አድርገዋል በሚል የወንጀል ክስ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ችሎቱ ተሰይሞ ሲቀርቡ ዳኛው «ካህናቱም ሆኑ የቤተክህነት ባለሥልጣናት ጳጳሱ አቡነ ቄርሎስም የጣሊያንን መንግሥት ገዥነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ እርስዎ ለምን ዐመፁ) ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ)» ሲል ጠየቃቸው፡፡ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በቆራጥነት «አቡነ ቄርሎስ ግብጻዊ ናቸው፤ ስለ ኢትዮጵያና ስለ ኢትዮጵያውያን የሚገዳቸው ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ኢትዮጵየዊ ነኝ፡፡ ሓላፊነትም ያለብኝ የቤተክርስቲያን አባት ነኝ፡፡ ስለዚህ ስለ ሀገሬና ስለ ቤተ ክርስቲያኔ እቆረቆራለሁ፡፡. . . እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ በእኔ ላይ የፈለጋችሁትን አድርጉ፡፡ ግን ተከታዮቼን አትንኩ» በማለት ሕያው በሆነ ቃላቸው መለሱ፡፡ ሰማዕተ ጽድቅ በሆነ ደማቸው አተሙ፡፡ አኩሪ በሆነ አባታዊ ሓላፊነታቸው ለአገር፣ ለቤተክርስቲያን፣ ለወገን ሁሉ አለኝታነታቸው አረጋግጠው በሰማዕትነት አለፉ፡፡ / መርሻ አለኸኝ/ዲያቆን/፣ 1996ዓ.ም፣ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን፣ገጽ.77/

ዛሬ ቤተክርስቲያንም ሆነች ቤተክህነቱ ያጣው ጴጥሮሳዊነት ይኽ ነው፡፡ በዘመናችን ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት ይኽን የጽድቅ ፍኖት ይዘው መጓዝ ሲሳናቸው አይተናል፡፡ እንደ አቡነ ጴጥሮስ የድህነት ቀንበር ለተጫነው፣ በችጋር አለንጋ ለተገረፈው፣ በሀዘን ለተቆራመደውና ለጎበጠው ሕዝባችን ሊቆረቆሩ ይቅርና አባታዊ ሓላፊነት ለሰጠቻቸው እናት ቤተክርስቲያን ጠበቃ መሆን ሲሳናቸው ተስተውሏል፡፡ ሁሉም በሰማዕተ ጽድቅ አቡነ ጴጥሮስ ዘመን እንደነበሩት ግብዊ ጳጳስ ሆነውባታል፡፡ በእርግጥም እውነት ነው፡፡ አንዳንዶቹ የአሜሪካ እና የካናዳ ዜግነት ኖሯቸው በአሜሪካ እና በካናዳ ከቀኖና ቤተክርስቲያን ውጭ የግላቸው ቤተክርስቲያን የከፈቱ ባዕዳን ናቸው፡፡ እዚው ያሉት በየስድስት ወሩ ከዲያስፖራው ምእመን በተወካዮቻቸው አማካይነት የተሰበሰበውን ገንዘብ ለመተሳሳብ እና የድርሻቸውን ለመውሰድ ወደ አሜሪካ ያመራሉ፡፡ በገንዘቡም ከአንድ አባት የማይጠበቅ ኢ-ሥነምግባራዊና ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶችን በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ይፈጽማሉ፡፡ ስለዚህ እንዴት ጴጥሮሳዊ ወኔ ይኖራቸው)

ሌሎቹም የቤተክርስቲያን አባት መሆናቸው እስኪጠፋን ድረስ ሀገረ ስብከታቸውን ትተው አዲስ አበባ በዘመናዊ ቪላ የሚሽሞኖሙኑ፤ እነርሱ በሀገረ ስብከታቸው ተቀምጠው የሚሆነውን ከመሥራት ይልቅ፤ ባለጉዳዮችን በየመኖሪያ ቤታቸው የሚያንከራትቱ፤ እንደ ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ሕዝባዊ አለኝትነታቸውን ከማረጋገጥ ይልቅ፤ ዘመናዊ ቤት የሠሩበትን፣ ዘመናዊ መኪና የገዙበትን፣ በየሳምንቱ ዶሮ፣ ቅቤ፣ ማር፣ በግ የሚያማርጡበትን ገንዘብ የሰጣቸውን ምእመን «ቤተክርስቲያን ተሳልመህ ከመመለስ ውጭ ምንም አያገባህም» ብለው የሚመጻደቁ ፊውዳሎች ናቸው፡፡ /ነጋድራስ ጋዜጣ፣ሐምሌ 30 ቀን 2002 ዓ.ም፣ቅጽ.07፣ቁጥር 240፣ገጽ.2/

አንዳንዶቹም ከቤተክርስቲያን ልዕልና እና መታፈር ይልቅ ራሳቸውን በአገረ ስብከቶቻቸው ልዑላን በማድረግ የሾሙ፤ የአክሊለ ሦክ ምሳሌ የሆነውን ቆብ ማድረጋቸውን ዘንግተው ዘውድ የደፉ ይመስል በዙርያቸው «እራት አግባዎችን» አደራጅተው ለቤተክርስቲያን የማኅፀን እሾኽ የሆኑ፤ የትኛውም አካል እነርሱን እስካልነካ ድረስ ቤተክርስቲያን ላይ «ቤንዚል አርከፍክፎ፣ ክብሪት ጭሮ እሳት ቢለቅ» አባታዊ መዓዛ የማይታይባቸው፤ ጴጥሮሳዊነት እጅጉን የራቃቸው ሥጋውያን ናቸው፡፡ እናም አንዱ ቤተ ክህነቱ ያጣው የቤ ተክህነት ጴጥሮስ እና ጴጥሮሳዊነት ይኽን ነው፡፡

3. ከመንኖ ጥሪት
መንኖ ጥሪት በዚህ ዓለም ያለን ማንኛውም ሀብትና ንብረት ንቆ መተው ነው፡፡ «ማንም ከእናንተ ያለውን ሁሉ የማይተው ደቀ መዝሙሬ ሊሆን አይችልም» እንዲል ሉቃ.14.33፡፡ እንግዲህ የዚህን ዓለም ጣዕም ማጣጣም ያልተወ መንፈሳዊ አባት የክርስቶስ ደቀመዝሙር ሊሆን ይቅርና ጥሩ ክርስቲያንም አይሆንም፡፡ እርሱ ምውት ሕሊና ነውና፡፡ የአቡነ ጴጥሮስ የሰማዕትነት ጥብዓት ምንጩ ይኸው መንኖ ጥሪት ነው፡፡ ፋሺስት ጣሊያን የእርሱ አቋም የራሳቸው አቋም፤ የእርሱ የጭቆና አገዛዝ የእርሳቸው አገዛዝ፣ የእርሱ ተራ ፕሮፓጋንዳ የእርሳቸው እውነት አድርገው እንዲቀበሉ መደለያ /ገንዘብ፣ መኪና በዘመኑ ዘመናዊ የሚባል ቤት/ ልስጦት ሳይላቸው ቀርቶ ነውን) ለሕዝባቸው፣ ለሀገራቸውና ለቤተክርስቲያናቸው ሰማዕት የሆኑት) እርሳቸው ግን መንኖ ጥሪትን ገንዘብ ያደረጉ አባት በመሆናቸው ሌሎቹ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት ለፋሺስት ጣሊያን ሲያድሩ መደለያው ሳያንበረክካቸው በመንፈሳዊ ወኔ ሰማዕት ሆነዋል፡፡

የዛሬዎቹ አንዳንድ ጳጳሳት የመንኖ ጥሪትን ሕይወቱን ይቅርና ቃሉን ማወቃቸውን እጠራጠራለሁ፡፡ ዛሬ፣ ዛሬ አንዳንዶቹ ለመኪና ስጦታ፣ ለገንዘብ መደለያ፣ ለውዳሴ ከንቱ ብለው እናት ቤተ ክርስተያንን ዋጋ እያስከፈሏት ይገኛሉ፡፡ ዶግማዋን በላንድ ክሩዘር፣ ቀኖናዋን በG+1,2,3,4 . . . . ቤቶች ለውጠዋል፡፡ ሥርዐተ አበውን አመድ ላይ የወደቀ ሥጋ አድርገዋል፡፡ ወርቅና ብር ለመዘነላቸው አጽራረ ቤተክርስቲያን ሁሉ የሚያድሩ እንዲሁም ጥብቅና የሚቆሙ፣ ጥሩ የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ ሆነው የሚያገለግሉ ናቸው፡፡

አንዳንዶቹም የጴጥሮሳዊነት ምንጭ የሆነው መንኖ ጥሪት እጅግ ስለራቃቸው በየገዳማቱ፣ በየአብያተ ክርስቲያናቱ ስም የሚሰበሰበው ገንዘብ የገዳማቱን እና የየአድባራቱን መሠረታዊ ችግር ከሚፈታ ይልቅ እነርሱ ኪስ ሲገባ የሚያስደስታቸው፤ በየሀገረ ስብከቶቻቸው ያሉ ሊቃውንት በችጋር ሲሰደዱ፣ ወንበር ሲያጥፉ እነርሱ ግን መደለያ ያቀረቡላቸውን አጽራረ ቤተ ክርስቲያንን ሲከባከቡ፣ ሽርጉድ ሲያበዙላቸው ይታያል፡፡ ከቤተክርስቲያኗ የአስተዳደር ሕግ እና ሥርዐት ውጭ በየሀገረ ስብከቶቻቸው የእኅት እና የአክስት ልጆቻቸውን የሚቆጥሩ፡፡ እነርሱም በአቅማቸው ቤተሰባዊ አስተዳደርን ያሳፈኑ ናቸው፡፡ ለምን) «ጥጃ ጠባ ሆድ ገባ» ነውና፡፡ ከዚህ እውነታ ተነሥተን እነርሱ በፓትርያሪኩ ላይ ያነሡትን የቤተሰብ አስተዳደራዊ በደልን ስንፈትሽ ሞራላዊ ብቃት እንደሌላቸው ማረጋገጥ እንችላለን፡፡ እነርሱም ቤተሰባዊ አስተዳደር ደዌ የተጣባቸው ናቸው፡፡

ለዚህም ነው፡- እኛ እያለን አጽራረ ቤተክርስቲያን አይነኩም ባዮች የሆኑት፡፡ እነርሱ ለቤተክርስቲያን መከራ ከሚቀበሉ ቤተክርስቲያን መከራ መቀበሏን የፈቀዱት፡፡ እነርሱ ሞት ከሚቀምሱ ሥርዓቷን፣ ዶግማዋን፣ ቀኖናዋን ለሞት የዳረጉት፡፡ በአንድ ጀንበር የበር መሰበር ብትንትናቸው ወጥቶ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍያው ቡድን ያስረከቡት፡፡ ከቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ እና ሰማያዊ ሥልጣን መከበር ይልቅ የአባ እገሌ መሻር እና የአባ እገሌ መሾም ጉዳይ ሆኖባቸው በፍቅረ ሢመት /በሥልጣን ጥም/ አብደው በቤተክህነቱም ሆነ በቤተ ክርስቲያኒቱ ማየት የሚገባንን የአስተዳደር ለውጥ እንዳናይ ግርዶሽ ሆኑብን፡፡

እንግዲህ ቤተክህነቱም ያጣው የቤተክህነቱ ሰው ጴጥሮስ እና የእርሱ ተክለ ሰብእና ነው፡፡ የእያንዳንዳችንም ውሳኔ የሚጠይቀው ይኽንን ለመመለስ ዝግጁ መሆን ላይ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችንም ሆነች ቤተክህነቱ ከገቡበት ማጥ ልናወጣቸው የምንችለው በጴጥሮሳዊነት ነው፡፡ አምላከ ጴጥሮስ ባዶዋን ለቀረችው ቤተ ክርስቲያናችን እንዲሁም የሰው ያለህ ለሚለው ቤተክህነት ያጣውን ሰው እስኪመልስለት እርሱ እንደፈቀደው ይሁን ከማለት ባሻግር ሁሉም ስለሁሉም በሁሉም የድርሻውን ይወጣ፡፡

Wednesday, July 20, 2011

“አን ዱ” የለም እንጂ “አን ዱ” ማ ቢኖር?

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብዙ ብዙ ፈተናወችን አልፋ እዚህ ለመድረሷ ጥርጥር የሌለው ሀቅ ነው በዘመናችን ያለው ፈተና ግን ስትራቴጂዎች በመቀየስ እስከ አሁን ካለው ኑፋቄያዊ አስተምሮ በተለየ መልኩ ቤተ ክርስቲያኗን ባለችበት ከእነ ምእመኗ እና ሕንፃዋ ሙሉ በሙሉ ፕሮቴስታንታዊ አድርጎ መውረስ የስልቱ የመጨረሻ ግቦች ነው የተለመዱ የተሐድሶ ስትራቴጂዎች፡ ‹‹አባቶችን መከፋፈል እና የአንዱ ደጋፊ የሌላው ነቃፊ መምሰል፣ የጥላቻ ጽሑፎችን በማሰራጨት ምእመናንን ማደናገር፣ ፖለቲካዊ ክሶችን ማቅረብ፣ ከገዳማት እናቶችን ማስኮብለል፣ የነጋዴዎች እና የብፁዓን አበው ደጋፊ መስሎ መቅረብ፣ ብዙ ውስጠ ወይራ የሆኑ የጽዋ ማኅበራትን መመሥረት፣ ጉባኤያትን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ እንዲካሄዱ እገዛ ማድረግ፣ በተቻለ መጠን የውስጥ ለውስጥ(Underground) ሥራዎችን በይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል(ለዚህም ከገድላት የተወሰኑ መቀበል)፣ የፎርጅድ ጽላት ዝግጅት፣ የሙዳየ ምጽዋት ብርበራ፣ የቤተ ክርስቲያን ቃጠሎ እና ንዋየ ቅድሳት ዘረፋ፣ የቤተ ክርስቲያንን ሕንጻ በግለሰብ ስም ማዛወር፤ የሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ አባል በመሆን፣ በከተሞች ታላላቅ ጉባኤያትን በማዘጋጀት በገዳማት እና አድባራት ስም ገንዘብ ማሰባሰብ እና ለግል ጥቅም ማዋል፣ ፎርጅድ ማኅተሞችን በማዘጋጀት በአባቶች ስም ልመና ማካሄድ፣ በባሕታዊነት ስም መነገድ እና አስነዋሪ ድርጊቶችን በአደባባይ እና ሰዉ በሚያይባቸው ቦታዎች በመፈጸም ሕዝቡ ባሕታዊ እና መነኩሴ እንዲጠላ ማድረግ፣ ገዳማት ውስጥ እየገቡ በተለያዩ ሰንካላ ሰበቦች ሁከት መፍጠር እና ጠብ አስነሥቶ የተወሰኑትን አስወጥቶ ይዞ በመጥፋት እነዚያን የመናፍቃን ሰለባ ማድረግ፣ ገዳማትንም መፍታት›› ምን አለ “ አን ዱ“ ቢኖር ይህን ኩሉ ጉድ ለመፈፀም የተዘጋጁትንና እየሄዱበት ያለውን አቅጣጫ ሁሉ አንድ ወደ ኋላ ብለንው የአባቶቻችንን አሰተምሮ እንዲሰብኩ ፎረማት ባረግናቸው ነበር ፡፡
“አን ዱ” ያው እንደምታውቁት በኮምፒውተር አጠቃቀም ለይ የ “አን ዱ” ጥቅም የማይረዳ የለምና አንድ ነገር ስንሳሳት የ “አን ዱ” ኮማንድ በመጠቀም የነበረውን እንዳልነበረ የደርገዋል ታዲያ ይሄ “አን ዱ” የሚባል ነገር እንደ ኮምፒውተር በኑራችንም ቢኖር ምናለበት ታዲያ ይህን አንዱ ተጠቅመን ኑፋቄውን እነዳለነበር ያለፉትን አበው ለእምነት ለተዋህዶ የቆሙትን እነደ ቅዱስ ቄርሎስ ያሉትን መልሰናቸው “ሥላሴ አትበሉ” ለሚሉት ለእነበጋሻው አይነቱ ይህን ምስጢረ ሥላሴን ከ ሀ ጀምረው ያስረዱት ነበር እንዲህም ብለው ምስጢረ ስላሴን “እግዚአብሄር በአካል ሶስት በባህርይ አንድ ብለን እናምናለን፡፡ይሄውም ፦ አንድ መለኮት ፣ አንድ ባህርይ ፣ አንድ ልእልና ፣ አንድ ጌትነት ፣ አንድ ክብር ፣ ከጥንት አስቀድሞ የነበረ አንድ ቀዳማዊነት ነው ፤ ደግሞም በሶስት አካላት ፣ በ ሶስት ገፃት ፍፁማን ናቸው ፣ ግዙፋን አይደሉም ፣ ያልተፈጠሩ ናቸው ፣ ድካም የማይስማማቸው የማይለወጡ ናቸው ፣ ለመገኘት ጥንት ለዘመን ፍፃሜ የላቸውም፡፡ ወልደ እግዚአብሄር ዳግመኛም ከአብ ባህርይ የተገኘ አምላክ ፣ ቃል ፣ ወልድ ፣ ያልተፈጠረ ፣በመለኮት አንድ ከሚሆኑ ከሶስቱ አካላት አንድ አካል ፣ ከአብ ጋር ትክክል የሚሆን ፣ አለም ሳይፈጠር በመለኮታዊ ልደቱ ከአብ የተወለደ ፣ ፍፁም እግዚአብሄር አብን በመልክ የሚመስለው ፣ በባህርይ የሚተካከለው የማይመረመረ የጌትነቱ መታወቂያ እንደሆነ እናምናለን፡፡ በገፁ በአካሉ ልዩ የሚሆን የአብ ልጅ ፣ አምላክ ፣ ቃል በአባቱ ፈቃድ ፣ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ለእኛ ቤዛ ሆኖ ተሰጠ፡፡ ያልተፈጠረ ፣ ስጋ ያልነበረው ፣ የማይለወጥ እርሱ እግዚአብሄር ቃል በማይመረመር ግብር በመልኩ ፣ በአምሳሉ የፈጠረንን እኛን ሰወችን ለማዳን ከአብ አንድነት ሳይለይ ከሰማይ ወረደ፡፡ ቃል ስጋ መሆን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ሲሆን ሰው ሆነ ፤ ከጌትነቱ ክብር ፈፅሞ አልተለየም ፤ ምንም ሰው ቢሆን እርሱ ከፍጡራን ሁሉ በላይ ነው ፤ በመለኮቱ ህግን የሰራ ሲሆን እነሆ ህግን በመፈፅም ተገኘ ፤ ህግን ሲሰጥ በነበረበት ባህርይውም ፀንቶ ኖረ፡፡ በመለኮቱ ገዢ ሲሆን የተገዢ ባህርይን ገንዘብ አደረገ ፣ ግን የጌትነት ክብር ከእርሱ አልተለየም ፤ አንድ ሲሆን ለብዙወቹ ምእመናን በኩር ሆነ ፤ በአንድነቱም ፀንቶ ኖረ፡፡ በማይመረመር ምስጢር እንደ እኛ በመሃፀን መፀነስን ወደደ ፤ እርሱ ሰው እንደመሆኑ በመሃፀን ሳለ በባህርይ መለኮቱ በሰማይ በምድር ፣ ከምድርም በታች ምሉእ ነው ፤ በማይመረመር በማይነገር ጌትነቱም በአብ እሪና ይኖር ነበረ ፤ የሕይወት እስትንፋስ ያላቸው ሁሉ በላይ በታች ያሉ ፍጡራንም ሁሉ በመሃል እጁ ናቸው ፤ አሽናፊ ፈጣሪ እርሱ እንደ ከሃሊነቱ ሁሉን ያዝዛቸዋል፡፡ መለኮትና ትስብእት በተመለከተ እግዚአብሄር ወልድ በድንግል መሀፀን ሳለ በሰማይም በምድርም ከአባቱ ጋር አንድ ባህርይ መለኮት ህልው ነውና ከሃጢአት በቀር በመሀፀን ሆኖ ከተፈጠረ ከፍፁም ትስብእት ጋርም በማይመረመር ባንድ ባህርይ መለኮት መቸም መች አንድ ነውና፡፡ እግዚአብሄር አብን በመልክ የሚመስለው ፣ በባህርይ የሚስተካከለው እርሱ ቀምቶ እግዚአብሄር የሆነ አይደለም ራሱን አዋርዶ የተገዥን ባህርይን ገንዘብ አደረገ እንጂ ፤ መለኮትስ እንደሰው በድንግል መሀፀን ያለ የእለት ፅንስ በመሆን በድንግል ማህፀን ሳለ በሰማይ በምድር ምሉ ነው፡፡ ደግሞ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በጥቂት በጥቂት ማደጉን ወንጌላውያን ፃፉልን ፦ በየጥቂቱ ያደገ ግን መለኮት አይደለም ፡ በሰማይም በምድርም የመላ ነውና ፤ በሁሉ በሰማይ በምድር የመላው እንዴት ያድጋል? ከተዋሃደው ስጋ ጋር አንድ አካል አንድ ባህርይ ነውና በየጥቂቱ ማደግን ገንዘብ አደረገ፡፡ ከሃጢአት ብቻ በቀር እንደ እኛ በስራው ሁሉ ተፈተነ ፣ ተራበ ፣ ተጠማ ፣ ደከመ ፣ አንቀላፋ ፣ በላ ፣ ጠጣ ፣ አለቀሰ ፣ ተከዘ ፣ አዘነ ፣ ታመመ ፣ ሞተ ፣ ተገነዘ ፣ በመቃብርም ተቀበረ ፤ ይህስ እንዴት ለመለኮት ይነገራል? ነገር ግን እግዚአብሄር ቃል በተዋሃደው ስጋ ስለእኛ ይህን ሁሉ ገንዘብ አደረገ፡፡ መለኮት ግን ከመከራ ሁሉ የራቀ ነው፡፡ (ወይንስ) በባህር ላይ ተራመደ ፣ ሙታንን አስነሳ ፣ ድውያንን ፈወሰ ፣ ከሞት ተነሳ ፣ በዝግ ቤት ገባ ፣ ወደ ሰማይ አረገ እንደምን ይባላል? ይህ የትስብእት ገንዘቧ አይደለምና ፣ ነገር ግን ሰውን ሰለመውደዱ የቃል ገንዘብ ለትስብእት ሆነ እንጂ ፤ እኛም ሰው አምላክ ሆነ ስለዚህ እንላለን፡፡ እንግዲህስ እግዚአብሄር ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋው ሞተ እንላለን እንጂ በባህርይው (በመለኮቱ) ከሞተስ እነሆ አብም ሞተ ደግሞ እንላለን ፣ እነሆ መንፈስ ቅዱስ ሞተ ደግሞ እንላለን ፤ ነገር ግን መለኮት ህማም ሞት ስለሌለበት እግዚአብሄር ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋው ሞተ እንላለን፡፡
አበው ባስረዱት ነበር ምን ያረጋል ታዲያ “አን ዱ“ በህይወታችን የለም እነጂ የቄርሎስ ትምህርቱ እንዲህ እንየው ታዲያ አልዛርን ከሞት ያስነሳው ማን ነው? ወይንስ እግዚአብሄር የሚለው ስም ከሶስቱ አካላት የማን ነው? እናንተ አልዛርን ከሞት ያስነሳው ኢየሱስ ነው እግዚአብሄር አይደለም የምትል እስኪ መልስልኝ ፦ ይህ ስም የአብ ብቻ ነውን? አባቶች እንዳስተማሩን ይህስ የሶስቱም የአንድነት ስማቸው ነው፡፡ እኛም እግዚአብሄር ስንል ፦ እግዚአብሄር አብ ፣ እግዚአብሄር ወልድ ፣እግዚአብሄር መንፈስ ቅዱስ ማለታችን እንደሆነ እናውቃለን፡፡ እስኪ መልሱልኝ ፦ አልዛርን ከሞት ያስነሳው ኢየሱስ ብቻ ነው የምትሉ መለኮትን ትከፍሉት ዘንድስ ማን አስተማራችሁ? ወይንስ ለስላሴ ስንት መለኮት አለው? ስላሴ ግን በባህርይው አንድ መለኮት እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ወይንስ ኢየሱስ ክርስቶስ አልዛርን ከሞት ያስነሳው በቃል ገንዘብ ነውን? ወይንስ በትስብእት ገንዘብ? ይህንስ የኢየሱስ ክርስቶስን ባህርይ ትከፍሉ እንደሆነ ጠየቅኳችሁ፤ ነገር ግን እግዚአብሄር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ በተዋህዶ አንድ እንደሆነ እኛ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች እናምናለን፡፡ እንግዲህ የቃል ገንዘብ ለትስብእት እንደሆነ በመለኮቱ ሰማይና ምድርን የመላ ፣ በስልጣኑ ሁሉን የፈጠረ እርሱ በመለኮቱ ስልጣን አልአዛርን ከሞት አስነሳው እንላለን ፤ የስላሴ መለኮትም አንድ ነውና ስላሴ ደግሞ አልአዛርን ከሞት አስነሳው እንላለን ፣ ይህም መለኮት የእግዚአብሄር አብ ነውና እግዚአብሄር አብ አልአዛርን ከሞት አስነሳው ደግሞ እንላለን፤ ለመንፈስ ቅዱስም ይህ ይነገር ዘንድ ይሆናል፡፡ መለኮት ከ ትስብእት ለአይን ጥቅሻ እንኳን እንዳልተለየው ፦ አንድ በሆነው መለኮት አብም መንፈስ ቅዱስም ወልድን በስራው ሁሉ አልተለዩትም ፤ እግዚአብሄር ወልድም ምንም ስጋን በመልበሱ በምድር ቢሆን በመለኮቱ ግን ከዙፋኑ አልተለየም፡፡እንዲህ ስንል ግን እግዚአብሄር አብ ሞተ እንላለንን? ወይንስ እግዚአብሄር መንፈስ ቅዱስ ተሰቀለ እንላለን? እስኪ መልሱልኝ መለኮት ይሞታልን? ይሰቀላልን? አይሞትም አይሰቀልምም ፤ ስለዚህም እግዚአብሄር አብ ፣ እግዚአብሄር መንፈስ ቅዱስ ፣ ወይንም ስላሴ ሞቱ አንልም፤ ነገር ግን እግዚአብሄር ወልድ በተዋሃደው ስጋ ስለእኛ ይህን ሁሉ ገንዘብ አደረገ ብለን እናምናለን ፡፡ እንግዲህስ ይህን አባቶች አስተማሩን ፤ እናንተ ግን አዲስን ትምህርት ከየት አመጣችሁት? እኛ ግን አልአዛርን ባስነሳው እግዚአብሄር እናምናለን፡፡ አበው ባስረዱት ነበር ምን ያረጋል ታዲያ “አን ዱ“ የለም እንጂ “አን ዱ“ ቢኖር እንደ በጋሻው ያለውን መምህር አበው አቃንተውት ልጁንም ፎርማት ባደረጉት ነበር፡፡
ያንን ወንድሞች በቅንነት እውነተኛ መስሎአቸው እናገለግልበታለን ብለው የገቡበትን ‹‹የቅድስት ማርያም የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ማኅበርም እነ በጋሻውና የሬድ አደመ ባልፈጠሩት ነበር ‹‹የቅድስት ማርያም የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ማኅበር›› - ይህ ማኅበር በቅርብ ጊዜ የተቋቋመ(እነ በጋሻው ደሳለኝ እና ያሬድ አደመ በዋናነት የሚሳተፉበት) ሲሆን የተቋቋመባቸው ዋና ዋና ዓላማዎች፡- (1)የትምህርት አሰጣጡን ይዘት ከመሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ይልቅ ግራና ቀኝ ወደማያስለይ እና መሠረታዊ ቁም ነገር ወደማያስጨብጥ ተራ ወግ እና ተረት መለወጥ ነው፤ የዚህ ተግባር ዓላማም ምእመኑ መሠረታዊ የሆነውን የቤተ ክርስቲያኑን አስተምህሮ እንዳያውቅና እንዲህ ከሆነም የሚጫንበትን ኑፋቄ ሳያቅማማ እና ሳይለይ እንዲቀበል ለማድረግ ነው፡፡ (2)የስብከተ ወንጌሉን አቅጣጫ ለቤተ ክርስቲያናችን ወካይ ዓርማ (Icon) የሚባሉትን ነገሮች የሚያጥላላ እና የሚያናንቅ ማድረግ ነው፡፡ በዚህም ሕዝቡ ለቤተ ክርስቲያን ያለውን አክብሮት እንዲቀንስ እና እንዲጥል ከዚያም በውስጡ ቤተ ክርስቲያኑን እንዲጠላ ማድረግ ነው፡፡ (3)ሃይማኖታዊ ልዩነቶችን ማጥፋት፤ ይህም ፕሮቴስታንታዊውን አስተምህሮ አሾልኮ በማስገባት ‹‹አንድ ነን፣ እዚህም እዚያም የሚሰበከው ጌታ ነው፤. . . ወዘተ›› በማለት ከውስጥ ሆኖ መለወጥ ነው፡፡ (4)የተለያዩ ማኅበራትን በሕዋስ(Cell) ደረጃ በየጉራንጉሩ መመሥረት እና ማቋቋም፤ እነዚህን ጥቃቅን ማኅበራት አህጉረ ስብከት ስለማያውቋቸው እና የሚቆጣጠሩበትም መንገድ ስለ ሌላቸው እነዚህ የሚያዘጋጇቸው ጉባኤያት፣ የሚጋብዟቸው ሰባክያን እና በዚያም የሚሰጠው ትምህርት ለዓላማቸው የተመቸ ይሆናል፤ እየሆነም ነው፡፡ (5) በስብከቶቻቸው እና በጽሑፎቻቸው የፕሮቴስታንቶችን ምንጮች መጠቀም፣ ለዚህም በቅርብ ጊዜ ያሳተሙት መጥሐፍ ሐሳቡ ብቻ ሳይሆን ርእሱ ሳይቀር የፕሮቴስታንት ፓስተር ከጻፈው መጽሐፍ የተወሰደ ነው፡፡ ታዲያ “አን ዱ “ በህየወታችን ቢኖር ኖሮ ሰለስቱ ምዕት አቕጣጫውን በእነሱ መስመር ባቃኑት ነበር ትምህርት ጤፉ በጋሻው ይህን ወደ መሰለው የ”እኔ ከሞትሁ ሠርዶ አይብቀል” ግዙፍ ድምዳሜ ለመድረስ በንጽጽሩ ምን ያህል ቦታዎችን በመነሻነት እንደወሰደ አይታወቅም፡፡ የሚታወቅ ነገር ቢኖር መምህረ ሃይማኖት ባሕታዊ ኀይለ ጊዮርጊስ የተባሉ ሰባኬ ወንጌል እንደተናገሩት፣ በጋሻው እና “የሞንታርቦ ወንድሞቹ” ትውልዱ ማንነቱን ለይቶ በማያውቅበት የምሽት ጉባኤዎች ድብልቅልቅ በማደንዘዝ ሀብቱን እየበዘበዙ፣ እናት ቤተ ክርስቲያኑን በፕሮቴስታንታዊ-ተሐድሶ-ኑፋቄ አዳክሞ ለመውረስ አልያም ከፍሎ ለመረከብ ላሰፈሰፉ ኀይሎች በሎሌነት እያገለገሉ መሆናቸው ነው፡፡ ታዲያ ይባስ ብለው ሰዎች በአውደ ምህረትህ ላይ ለፀሎት ተሰብስበው በ "እግዚኦ መሃርነ ክርስቶስ" አንተን በሚማፀኑበት ወቅትም፥ ፍፁም በሚያውክና በእልህ በተሞላ ድምፅ መዝሙር ለመባል ስርዓት በጎደለው ጩኧት ቤትህን አመሱት። አማኙንም ከአምልኮ ስርዓቱ ለማስተጓጎልና ቤትህ በመታደስና በመፅዳት ላይ መሆኑን የሚያሳይ ምሳሌ ለማኖር አፀድህን በሚቃጠል ቆሻሻ ጢስ አጠኑት። “አን ዱ “ ቢኖር ኖሮ! በሰጠሀቸው ፀጋ በፊትህ ተመፃደቁ፤ ትምክህታቸውም ፈር ለቀቀና በሀሰት ትምህርታቸው ህዝብህን አደናገሩት። በመንደር ወሬና ስድብ አስመርረውም አስለቀሱት። በገዛ ደምህ የዋጀሀትን ቤተ ክርስቲያን ‘አርጅታለች’ አሉና ለእድሳቱ ሚስማርና መዶሻ ለመዋዋስ ከመናፍቃን ጋር መከሩ። አረጀች ያሏትን ቤተክርስቲያንም በሣራ መሰሏት፤ እነሱም በስተርጅና የተወለዱ የሣራ ልጆች መሆናቸውን አበሰሩን። “አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ፥ በጽቅድቅ ጨለማ መብራቱ ይጠፋል።” (መጽሐፈ ምሳሌ 20:20) የሚለውን የወንጌል ቃል ስተውት ይሁን ንቀውት፥ በ40 እና በ80 ቀን የእግዚአብሄር ልጅነትን ያገኙና ቤተክርስቲያንን ያውቁ ዘንድ እንኳን ያልከለከሉዋቸውንና፥ ሀገርንና ሀይማኖትን ከጠላት ጠብቀው ያቆዩላቸውን አባቶች "የእንጨት ሽበቶች፣ ፍንዳታዎች" ብለው ለቀለለ ስድብ አፋቸውን ከፈቱ መንፈስ እንዳዘዘን እናስተምራለን” ከሚል “የዘመኑ ሐዋርያ ነኝ” ባይ ምእመኑ ምን ይማራል? “ንጉሣችን ቅልጥ አድርጎ ይዘምራል፤ አባባ ሲተኛ እኛ እንነቃለን፣ እኛ ስንተኛ እርሱ ይሠራል፤ ሥላሴ ሲያጫውቱ ያሥቃሉ፣ እሺ፤ በጣም ነው የሚያጫውቱት፤ ተባበሩኝ ብለው የሚያሥቁ ኮሜዲያን አሉ፤ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ እንደዛ አይደሉም፤ ለማርያም ከበሮ አይመታም ለጌታ እንጂ፤ ከጸበሉ ይልቅ የሚያጽናናቸው ቃሉ ብቻ ነው፤ በአንድ ወቅት በራስ ቅል ኮረብታ ላይ ኢየሱስ እና ዲያቢሎስ ቁማር ተጫወቱ…ዲያቢሎስም በጨበጣ ገባ፤ እኛ ሕዝቡን ጨፍረን እናምጣው፣ እናንተ መዝሙር አስተምሩት፤ እኛ ሕዝቡን ደንሰን እናምጣው፤ እናንተ ሥርዐት አስተምሩት፤ እኛ ሕዝቡን ጨፍረን እናምጣው እናንተ ሃይማኖት አስተምሩት፤ ይሄ ሕዝብ እኛ ሳንወድቅ ወድቋል፤ እኛ የምናምነው በፈውስ፣ በዝማሬ በጸጋ ነው፤ ‹በተሰጠኝ ጸጋ ሰይጣን ፎቶዬን ሲያይ መጮህ ጀምሯል› [ጋሞጎፋ ሳውላ ኪዳነ ምሕረት]” የሚል ሰባኪ ነኝ ባይ ዋልጌ የግል ተክለ ሰብእናውን ከመገንባት ውጭ እንደምን ምእመኑን በሃይማኖቱ ለማጽናት ይቻለዋል? ታዲያ ምን ያረጋል በዚህ ሁሉ ነገር “አን ዱ” ቢኖር ኖሮ አበውም በመጡ ታሀድሶም በጠፋ ነበር አምላክ ሆይ በጎችህ በተኩላዎች እንዳይነጠቁብህም የተኩላዎቹን አፍ ዝጋ፤ የበጎችህንም ንቃት አብዛ። የአሳቾቹም የጨለማ ጉዞ “እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው።” (ወደ ሮሜ ሰዎች 1:28) እንደሚለው ያንተው ፈቃድ ከሆነም፤ እባክህ ስለቅዱሳን ብለህ የዚህችን ቤተክርስቲያን ጥፋት አታሳየን ልቦናቸውንም አብርተህ ዳግም አንተን ያውቁ ዘንድ ይሁን።

Thursday, June 23, 2011

እውን ‹‹ተሐድሶ›› የለምን?

ሰሞኑን በተደጋጋሚ ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም ማኅበረ ቅዱሳን የፈጠረው ወሬ ነው!›› የሚል ንግግር በመስማቴ ይህንን አጭር ማሳሰቢያ ለመጻፍ ተነሳሣው፡፡ በእርግ...ጥ ንግግሩን ቀደም ሲልም ሰምቼው አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን መደጋገሙ ሲበዛ በተለይም ግምት የሰጠዋቸው ሰዎች ነገሩን ተቀብለዉት ስመለከት ለካ የሚናቅ ሐሰት የለም አሰኘኝ! ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን የፈጠረው ወሬ ነው!›› ለሚለው ለምን ፈጠረው? ይህን ሐሳብ ፈጥሮ ምን ይጠቀማል? ቢፈጥረውስ እናንተ ተሐድሶ ካልሆናችሁ ምናችሁ ይነካል?  የሚል የራሴን ጥያቄ ፈጥሮ ከመጠየቅ በቀር እኔን ስለማይመለከተኝ የማኅበሩ የቤት ሥራ ነውና ራሱ ይጨነቅበት ብዬ አልፌዋለሁ፡፡ ትንሽ ማብራሪያ ለመስጠት የምሞክረው ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም›› በሚለው አመለካከት ላይ ነው፡፡ በእርግጥ አንድን ነገር እያለ ‹‹የለም›› ማለት አንድም ሐሰት ዳግመኛም የጥፋት ስልት መሆኑ ይታወቃል፡፡ የአጥፊዎች ሁሉ አውራ የሆነ ሰይጣንም ይህን ስልት በተለያየ መንገድ ሲጠቀምበት ይታያል፡፡ ሰይጣን በሰዎች ልቡና ያድርና ራሱን ደብቆ ክፉ ሥራ ሲያሠራቸው ይኖራል፡፡ በወንጌል እንደተነገረው በጾም፣ በጸሎትና በመንፈሳዊ ሥራ እንዲሁም በተቀደሰ ውሃና አፈር (በጸበል) ኃይሉ ሲደክምበት ‹‹ተቃጠልኩ›› እያለ ይለፈልፋል፡፡ በዚህ ጊዜ ሰይጣን መሆኑ ታውቆ አስፈላጊውን መንፈሳዊ ሥርዓት በማከናወን ያንን ሰው ለቆ እንዲወጣ ይገሠጻል፤ ይረገማል፤ ይገዘታል፡፡ ወዲያውም ለቆ ይሄዳል፡፡ ክርስቲያኖች ይህን የሰይጣን ክፋትና አሠራር ያውቃሉ፡፡ ይሁን እንጂ በእግዚአብሔር መኖር የማያምኑ ከሃዲዎች በሰይጣን መኖርም አያምኑም፡፡ ሰይጣን እነዚህን ሰዎች እኔ ‹‹የለውም›› እያለ ይዘብትባቸዋል፤ ይዋሻቸዋል፡፡ እነርሱም በጸበል ሲለፈልፍ አይተው በሥራህ ተገለጥክ፤ አወቅንብህ እንዳይሉት እንኳን ይህ እኮ ጭንቀት ነው፤ ቅዠት ነው፤ ኢሉዥን ነው /illusion/፤ ኮንፍዩዥን ነው /Confusion/ ወዘተ እያለ ምክንያት በመደርደር አለመኖሩን ሊያሳምናቸው ይጥራል፡፡ በዚህም ሐሳቡን የተቀበሉት በርካቶች ናቸው፡፡ ይገርማል! ሥራው እየታየ፤ ንግግሩ እየተሰማ የለውም ማለቱ አቤት የሰይጣን ድርቅና! የተሐድሶ አራማጆች ሥራ ዓይኑን አፍጥቶ ጥርሱን አግጥጦ በሚታይበት በዚህ ዘመን ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የፈጠራ ወሬ ነው እንጂ በእውን ያለ ነገር አይደለም›› ማለት አንድም አይኔን ግንባር ያድርገው ከማለት ይቆጠራል፡፡ ወይም ደግሞ ከላይ በምሳሌ እንደተጠቀሰው አቅጣጫ የማስቀየር የቅሰጣ ተግባር ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ሌላው ቢቀር ፊደል የለየና ማንበብ የሚችል ሰው ከአንድ አሥር ዓመት ወዲህ የወጡትን በተመሳሳይ ርእሰ ጉዳዮች የተጻፉትን የሕትመት ውጤቶች ከሁሉም አቅጣጫ ቢከታተል ‹‹ተሐድሶ›› በቀናች ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ዶግማ ቀኖና እና ትውፊት ላይ ያነጣጠረ በጥናት የተቀነባበረ የጥፋት ስልት እንጂ  ጭራቅን የመሰለ የፈጠራ ወሬ አለመሆኑን በቀላሉ ይረዳል፡፡ ‹‹ተሐድሶዎች›› ራሳቸው የቁርጥ ቀን መድረሱን እያወጁ ወደ አደባባይ ሲመች በቃልና በጽሑፍ ሳይመች ደግሞ በጉልበት ጭምር እየተጋፉ ለመውጣት በሚሽቀዳደሙበት በዚህ ጊዜ ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር›› የለም ማለት ከ‹‹ተሐድሶነት›› የከፋ የሐሰት ምስክርነት ነው፡፡ በአገራችን የከተማና የገጠር ጎዳናዎች ላይ ሲመላለስ ‹‹…የተሐድሶ ቤተ ክርስቲያን›› የሚል ጽሑፍ እያነበበ ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም›› የሚል ሰው ምን ሊባል ይችላል? የማያውቅ ሰው የዚህኛው ከዛኛው ልዩነቱ ምንድር ነው? አንድ ናቸውን? እያለ ይጠይቃል እንጂ በማያውቀው ነገር ደፍሮ ምስክርነት አይሰጥም፡፡ በዛሬ ጊዜ ‹‹ተሐድሶአዊ እንቅስቃሴ የለም›› ማለት በሚቃጠል ቤት ውስጥ ጭስ አፍኖት እየሳለ በር ዘግቶ እንደመቀመጥ ይቆጠራል፡፡ ዛፍ በፍሬው እንደሚታወቅ ‹‹የተሐድሶ እንቅስቃሴም›› መገለጫዎች አሉት፡፡ እነዚያን እየመረመሩ ‹‹እንግድዳ ትምህርት›› (ዕብ13.9) ሲያገኙ መለየት እንጂ ‹‹ተሐድሶ የት አለ?›› ‹‹ተሐድሶዎቹስ እነማን ናቸው?›› የሚል ዓይነት ያልበሰለ አጠያየቅ ከእውነታው እንድንርቅ ሊያደርገን ይችላል፡፡ በየመንፈሳዊ መድረኮች ላይ ሁለት ዓይነት ልሣን ማድመጥ እየተለመደ መጥቷል፡፡ የቱ ‹‹እንግዳ ትምህርት›› እንደሆነ የእረኛቸውን ድምፅ የሚሰሙ እውነተኛ በጎች ለይተው ያውቁታል፡፡ የሴት ድምፅ ከወንድ እንደሚለይ ልዩነቱ ጉልህ ነውና፡፡ ዕረፍት የማይሰጡ፤ የቃላት ድርደራዎችና ጩኽቶች ከማሳመን እና ጥያቄን ከመመለስ ይልቅ ሌላ ጥያቄ የሚያጭሩ፣ የሚያጠራጥሩና የሚያስጨንቁ ስብከቶችና ‹‹መዝሙሮች›› የምን ነጸብራቅ ናቸው? ከአንድ የተሰወረ ምንጭ ካልቀዱትስ በቀር ብዙ ሰዎች አንድ ዓይነት ዘይቤ፣ ቃላት፣ ድምፅና እንቅስቃሴ ሊኖራቸው እንዴት ይችላል? በዚሁም ላይ ይህ ሁሉ ደግሞ ከመናፍቃኑ ጋር አንድ መሆኑ ምን ይጠቁማል? ‹‹ከተሐድሶ›› ስልቶች አንዱ በስውር መንቀሳቀስ ነው፡፡ ይህ በጥናትና በዓላማ የሚተገበር በመሆኑ በማስተዋል ካልሆነ በፍጥነት ለመለየት ያስቸግር ይሆናል፡፡ ይሁን እንጂ የአንድን ተክል ምንነት ለይቶ ለማወቅ ቅጠሉንና ፍሬውን ማየት ብቻ በቂ ነው፡፡ ለዚህም ገበሬ መሆን አይጠይቅም፡፡ ይህ ኮክ ነው፤ ይህ ወይን ነው፤ ይህ በለስ ነው! ለማለት ቆፍሮ ሥሩን የሚያይ የለም፡፡ ሥሩ በምክንያት ከመሬት ውስጥ መቀበሩ ይታወቃልና፡፡ ሥሩ ምንም ይሁን ምን የተክሉን ዓይነት ለይቶ ለማወቅ ቅጠሉንና ፍሬውን ማየት ብቻ በቂ ነው፡፡ እንደዚሁም የ‹‹ተሐድሶ እንቅስቃሴ›› መራራ ፍሬው በስሎ አዝመራውም ነጥቶ እየታየ ነውና ልብ ያለው ልብ ይበል! ‹‹ተሐድሶ የሚባል የለም›› እያሉ ስለማያውቁት ነገር ምስክርነት ከመስጠት፤ ለጥፋትም ሥራ ተባባሪ ከመሆን፤ ራስንና ሌሎችንም ከመጉዳት የሚቀድመው አፍን መሰብሰብና ራስን መመርመር ነው፡፡ ‹‹የተሐድሶ›› ሴራ ስውር እንደመሆኑ መጠን የዚህ የጨለማ ሥራ ሰለባ ከሆኑና ያላመኑበት ጉዳይ ከሆነ ይህንንም እውነት ዘግይተው ከተረዱ የሚሻለው ቶሎ መመለስ ነው፡፡ ‹‹ተሐድሶ የሚባል የለም›› ማለት ራስን የሚያድን መንገድ ስላልሆነ ከወዲሁ ንስሐ መግባት ይገባል፡፡ እንዲያውም ሌሎች እንዳይጠፉ መረጃ መስጠትና ካገኙት ልምድ በማካፈል አካሄድን ማሳመር እንጂ ‹‹ካፈርኩ አይመልሰኝ›› ዓይነቱ ድርቅና የሚበጅ አይሆንም፡፡ ነቢዩ እንደተናገረ ‹‹ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቅቃሉና›› (1ሳሙ2.10) ስንዴ ከእንክርዳድ ጋር በመመሳሰሉ እንደ አረም ተቆጥሮ አብሮ ቢነቀል እህል ስለሆነ ግዕዛን የለውምና አይፈረድበትም፡፡ ማለትም ማን ከእንክርዳድ ጋር ተሰለፍ አለህ? አይባልም፡፡ ክርስቲያን ግን ከመናፍቃን ጋር ቢሰለፍና አብሮ ቢቆጠር ራሱን አልለየምና ወቀሳ አይቀርለትም የሚገባው ነውና፡፡ ከክፉዎች ጋር አብሮ እንዳይፈረድበት የፈለገ እንደሎጥ ተለይቶ መውጣት ይገባዋል፡፡   በነገራችን ላይ ‹‹ተሐድሶ የሚባል ነገር የለም›› የሚለውን ሐሳብ ይዞ ሙጭጭ ማለት ምእመናንን እንዳይነቁ የማደናገሪያና የማዳከሚያ ስልት ካልሆነ በቀር ለምን ይጠቅማል? እንኳን ኖሮ ባይኖር እንኳን የሰባኪና የካህን ድርሻው እንዲህ ያለ ፈተና ሊከሠት ወይም ሊኖር ይችላልና ተጠንቀቁ እያሉ ምእመናንን ማንቃት እንጂ ‹‹ምንም የሚመጣ ችግር የለም›› እያሉ ማስነፍ አይደለም፡፡ ስለዚህ በገሃድ የሚታየውን እንቅስቃሴ ሽምጥጥ አድርጎ መካድ ከጤናማ አእምሮ የሚመነጭ አይደለም፡፡ ‹‹ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምህርት አትወሰዱ›› ዕብ13.9 ይቆየን! by Hibret Yeshitila

አበው ይናገሩ

እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ

የምንኩስና ግብር ምን ነበር ሚስጢሩ

የክርስቲያን ህይወት ምን ነበር ተግባሩ

መቃብሩን ክፈቱት አበው ይመስክሩ

እኔስ ሰው አማረኝ የሃይማኖት ጀግና

ወልድ ዋህድ ብሎ በእምነቱ የፀና፡፡

ጀግና ሰው አማረኝ ጠላት አሳፋሪ

ንጽህት ድንግል ብሎ እምነቱን መስካሪ

ነቢያት በመጋዝ የተሰነጠቁት

ሀዋርያት ቁል ቁል የተዘቀዘቁት

ሰማእታት በእሳት የተለበለቡት

ቅዱሳን ገዳም ደርቀው የተገኙት

ሚስጥሩ ምን ነበር አበው ይናገሩት፡፡

ይናገር ዝቋላ ጊሸን ላሊበላ

የቅዱሳንን አጽም ለምን እንዳልበላ፡፡

ዋልድባ ይናገር ዜጋመልም ሳይቀር

እንባቸው መፍሰሱ ለምን እንደነበር፡፡

ነበር ወይ ፈልገው ሹመት ሽልማት

ወይስ ሃብት ንብረት የተሟላ ቤት

ወይስ አምሯቸው ነው ፈልገው መሞት

እናንተ ገዳማት ምስጢሩን አውሩት፡፡

ጎበዝ ሰው አማረኝ በእምነቱ የፀና

ምግባር ሃይሞኖቱን በእጅጉ ያቀና፡፡

እንጦንስ የወለደው በምግባር በእምነት

ተምሮ ያደገ ከተክለሃይማኖት፡፡

የጊዮርጊስ ወዳጂ የት ነው የሚገኘው

በመሃል ከተማ በአራዳ ውስጥ ነው

ወይስ በዝቋላ በደብረ ሊባኖስ በደብረ ዳሞ ነው፡፡

ወገን ሰው ናፈቀኝ አይኔን ሰው አማረው

የሃይማኖት ጀግና የት ነው የማገኘው?

ልጋባ ወይ ዋልድባ ጫካ ካለበት

ማህበረ ስላሴ ከቅዱሳ ቤት

አክሱም ጊሸን ማርያም ከቃልኪዳን ቦታ

ይገኛል ወይ ጀግና ጠላት የሚረታ፡፡

ፈርሃ እግዚአብሔር በልቡ ያደረ

ቤተክርስቲያንን ያልተዳፈረ

የት ነው የሚገኘው ለሃይማኖቱ ሟች

ለተዋህዶ እምነት ጠበቃ ተሟጋች

የወገን መመኪያ የከሃዲ መቅሰፍት

ማነው እሱ ጀግና ተኝቶ እንደሆነ ይነሳ ቀስቅሱት

እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ

የምንኩስና ግብ ምን ነበር ምስጢሩ

የክርስቲያን ህይወት ምን ነበር ተግባሩ

መቃብሩን ክፈቱት አበው ይመስክሩ፡፡

ወገን ሰው ናፈቀኝ አይኔን ጀግና አማረው

በእምነት የፀና የት ነው የማገኘው፡፡

ወልድ ዋህድ ብሎ በእምነቱ የፀና

ብቅ ይበል እንየው እሱ ማን ነው ጀግና

በጎችን ከተኩላ ነቅቶ የሚጠብቅ

መከራ ቢከበው ከቶ የማይሰቀቅ

የሃይማኖት ጀግና ቆራጥ ሰው ገበሬ

እንደዚያ እንደጥንቱ ይገኛል ወይ ዛሬ፡፡

የወገን የዘመድ ጥቅም ያላወረው

የመናፍቆች እጅ ኪሱን ያልዳበሰው

የዓለም ደስታዋ ልቡን ያልማረከው

የክርስቶስ ወዳጅ እሱ ጀግና ማነው?

ምስጢርን ከምስጢር አንድ አድርጎ ተምሮ

ወልድ ዋህድ ብሎ ሃይማኖት መስክሮ

እንጦንስን መቃርስን በልቡ ያኖረ

ከጳውሎስ ከቄርሎስ ጥበብ የተማረ፡፡

ድንግል እመቤቴ ብሎ የሚመሰክር

መሆኗን የሚያምን ማህደረ እግዚአብሔር

ቋቅ እንትፍ ብሎ የጠላ ክህደትን

ትንታግ ምልስ ጭንግፍግፍን

ልሣነ ጤዛ መናፍቅን

ወልደ አርዮስነ ዲቃላውን

በሰይፈ ሥላሴ የሚቀላ

ጀግና ማን ነው ብቅ ይበላ፡፡

ነበር ወይ ያን ጊዜ ለሹመት መጓጓት

እስኪ ጎርጎርዮስ ይምጣና ጠይቁት፡፡

ፍቅርንም ይጠየቅ አባ ሕርያቆስ

ምስጢርን ጠባቂ ወይም አባ መቃርስ

የክርስቶስ ባሪያ የአጋንንት መቅሰፍት

ወንጌል አስተማሪ የሃይማኖት አባት

ይህንን ጉድ እንዲያይ ይምጣ ተክለሃይማኖት

የፀሎት ገበሬ ገብረመንፈስ ቅዱስንም ይነሳ ቀስቅሱት

ይነሳ ጊዮርጊስ ይመስክር ምስጢር

የሃይማኖት ፍቅር ምን እንደነበር፡፡

ከእናቶቻችንም አሉ ለፍጥረት ያዘኑ

ዲያቢሎስ እንዲማር ጌታን የለመኑ

ስንቱን ልዘርዝረው የአባቶችን ሙያ

እመር ብለው የወጡት ከስጋ ገበያ

ፆም ፀሎት ነበር የሃይማኖት ጋሻ

እንደ መስኖ ውሃ ከነዱት መነዳት

አላማው ምንድን ነው የዘመኑ ወጣት፡፡

እኔስ ሰው አማረኝ በእምነቱ የፀና፡፡

ዐይኔን ሰው አማረው ጀግና ሰው ገበሬ

ሃይማኖት መስካሪ እንደ ጥንቱ ዛሬ፡፡