Tuesday, December 18, 2012

መንግሥት አቡነ ማቲያስ ዘኢየሩሳሌምን 6ኛው ፓትርያርክ ማድረግ እንደሚፈልግ ታወቀ


  • ምእመናን “ቅዱስ አባታችን” ብለው በሙሉ ልብና በፍቅር የሚታዘዙት አባት ይፈልጋሉ፤
  • ቤተ ክርስቲያን “እንቁላልና ቲማቲም የሚወረወርበት ሌላ ፓትርያርክ” አያስፈልጋትም፤
(ደጀ ሰላም ታኅሣሥ 9/2005 ዓ.ም፤ ዲሴምበር 18/2012)፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፕትርክና በ5ኛው ፓትርያርክ አረፍተ ሞት ባዶ ከሆነ ወዲህ ላለፉት 20 ዓመታት ሲያከራክር የነበረው ርዕሰ ጉዳይ እንደገና፣ እንደ አዲስ መወያያ መሆን ጀምሯል። በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃም፣ በግል ደረጃም የተለያዩ ሐሳቦችም በመንጸባረቅ ላይ ይገኛሉ። በምእመኑ ደረጃ “ነገረ ፓትርያርክ”ን ከማንሣት በፊት ዕርቀ ሰላሙ መቅደም አለበት የሚለውን አበክሮ በማቅረብ ላይ ይገኛል። የተለያዩ ደብዳቤዎችንም ለሚመለከታቸው አካላት በሙሉ አቅርበዋል። በሁሉም በኩል ሥጋት የሆነው ግን ክንደ-ፈርጣማው፣ እጀ ረዥሙ የኢሕአዴግ መንግሥት ለእምነቱ ተከታዮች ፍላጎት ሳይገዛ “የራሱን ፓትርያርክ” እንዳያስቀምጥ ነው።
በጥቅምት 6/2005 ዓ.ም ዘገባችን እንደገለጽነው በመንግሥት በኩል የመጀመሪያ የፓትርያርክ ምርጫው የምሥራቅ ሸዋ ሀገር ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አቡነ ጎርጎርዮስ ሲሆኑ ይህ ካልሆነ በሁለተኛ ደረጃ የያዛቸው በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማትያስ መሆናቸው በብዙዎች ዘንድ የታመነ ነገር ሆኗል፡፡ የቀድሞው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ለአንዳንድ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት እንደ እንደራሴያቸውም እንደተተኪያቸውም አስተዋውቀዋቸው ነበር የተባሉት የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ስድስተኛ ፓትርያርክ ይኾኑ ዘንድ መንግሥት ወስኖ መግፋት ጀምሮ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ እንደ ምንጮቻችን ማብራሪያ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ወደ ፕትርክናው መንበር መገፋታቸው÷ “የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን አቋም እና አሠራር (እነርሱ ራእይ ይሉታል) ያስቀጥላሉ፤ ለመንግሥት ለመታዘዝና ፍላጎቱን ለማስፈጸም ይመቻሉ” በሚል ሐሳብ ነው ተብሏል፡፡

Saturday, December 15, 2012

በዋልድባ ስቃዩ እና እንግልቱ ቀጥሏል

በዋልድባ ገዳም አካባቢ መንግሥት የተለያየ ሙከራዎችን እያደረገ እንደሚገኝ እና በገዳማውያኑ ላይ ስቃዩን እንደቀጠለ ይነገራል። ባለፈው ወር ላይ የገዳሙን አባቶች ጥቂት የመንግሥት ባለሥልጣናት ሰብስበው እንዳነጋገሯቸው እና ለጥር ፬ ቀን ቀጠሮ ሰጥተዋቸው እንደተበተነ ይታወሳል። በመጪው ጥር ፬ ቀን ምን ሊመጣ እንደሚችል በገዳማውያኑ ላይ ሊደርስባቸው የሚችሉትን፣ እንደ መንግሥት ባለሥልጣኖች አባባል በጥር ፬ ቀን በሚደረገው ስብሰባ ላይ የመንግሥት ተወካዮች ለገዳሙ አባቶች "ለቦታው ካሳ ተቀበሉ አለበለዚያ ሌላ ነገር ይመጣል" በማለት ገዳማውያኑን ለማስፈራራት ቢሞክሩም፥ ገዳማውያኑም "ሞትም ቢመጣ እኛ የአባቶቻችንን ርስት አሳልፈን አንሰጥም፣ እኛን ገላችሁ ሥራችሁን መስራት ትችላላችሁ" በሚል ሁኔውን እየተጠባበቁ ይገኛሉ።

በዋልድባ ስቃዩ እና እንግልቱ ቀጥሏል

 በዋልድባ ገዳም አካባቢ መንግሥት የተለያየ ሙከራዎችን እያደረገ እንደሚገኝ እና በገዳማውያኑ ላይ ስቃዩን እንደቀጠለ ይነገራል። ባለፈው ወር ላይ የገዳሙን አባቶች ጥቂት የመንግሥት ባለሥልጣናት ሰብስበው እንዳነጋገሯቸው እና ለጥር ፬ ቀን ቀጠሮ ሰጥተዋቸው እንደተበተነ ይታወሳል። በመጪው ጥር ፬ ቀን ምን ሊመጣ እንደሚችል በገዳማውያኑ ላይ ሊደርስባቸው የሚችሉትን፣ እንደ መንግሥት ባለሥልጣኖች አባባል በጥር ፬ ቀን በሚደረገው ስብሰባ ላይ የመንግሥት ተወካዮች ለገዳሙ አባቶች "ለቦታው ካሳ ተቀበሉ አለበለዚያ ሌላ ነገር ይመጣል" በማለት ገዳማውያኑን ለማስፈራራት ቢሞክሩም፥ ገዳማውያኑም "ሞትም ቢመጣ እኛ የአባቶቻችንን ርስት አሳልፈን አንሰጥም፣ እኛን ገላችሁ ሥራችሁን መስራት ትችላላችሁ" በሚል ሁኔውን እየተጠባበቁ ይገኛሉ።

Wednesday, December 12, 2012

Monday, December 10, 2012

ዕርቀ ሰላሙ በሚቀጥለው ጥር ወር በሎስ አንጀለስ በድጋሚ ይካሄዳል

 (ምንጭ:- ደጀ ሰላም )፦ ከኅዳር 26 እስከ 30 (ዲሴምበር 5-9/2012) በሰሜን አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ከተማ ሲካሄድ የሰነበተው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት ለመፍታት የተደረገው ሦስተኛ ዙር የዕርቅ ድርድር እሑድ ኅዳር 30,2005 ዓ.ም መግለጫ በማውጣት እና ለሌላ ጉባዔ ቀነ ቀጠሮ በመስጠት ተጠናቋል።
በአገር ውስጥም ሆነ በውጪ ባሉ አባቶች እና ምእመናን ዘንድ በጉጉት የሚጠበቀው የአራተኛው ፓትርያርክ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ጉዳይ ዋነኛው የመነጋገሪያ አጀንዳ በሆነበት በዚህ ጉባዔ ከሁለቱም ወገን የተለያየ ሐሳብ ከመቅረቡ አንጻር ለጊዜው ከስምምነት ላይ የተደረሰበት አይመስልም።

ከአገር ቤት የመጣው ልዑክ “ቅዱስነታቸው በመረጡት ቦታ በጸሎት ተወስነው ይቀመጡ” ሲሉ በውጪ የሚገኙት አበው ደግሞ “ከነሙሉ ማዕረጋቸው ወደ መንበራቸው ይመለሱ” የሚለውን ሐሳብ አቅርበዋል። በሁለቱም በኩል ሐሳቡ ዕልባት ሳይሰጠው ቀርቷል።


በመግባባት፣ በመከባበር እና በመደማመጥ ተደርጓል በተባለው በዚህ በአባቶች ውይይት ከቀደሙት ሁለት ጉባዔያት በተሻለ “ተስፋ ሰጪ” የአንድነት ምልክቶች የታዩበት መሆኑን ብዙዎች እየመሰከሩ ነው። ሙሉ መግለጫው በዳላስ ደ/ም/ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በምዕመናን ፊት በተነበበበት ወቅት ከሁለቱ ወገን የመጡ ልዑካን ኮፒውን በእጃቸው ይዘው ታይቷል። በዕለቱ የተነበበው መግለጫ በዋነኝነት በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ሐሳብ ሰጥቶ ያለፈ ሲሆን እኛም እንደሚከተለው ጨምቀን አቅርበነዋል።

አጆራ ተክለ ሐይማኖት

ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ በአንቺ የተደረገው ነገር ድንቅ ነው! መዝ.86፥3

በመ/ር መንግስተ አብ ፡አበጋዝ
 
የሶርያው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም የምስጋና መጽሐፉ ‹‹ነቢያት ድንቅ ድንቅ ነገርን ተናገሩልሽ›› በማለት ስለ ወላዲተ አምላክ የተሰጡ ምስክርነቶች ድንቆች መሆናቸውን መስክሯል፡፡ ከዛሬ 3000 ዓመት ገደማ ቀደም ብሎም ነቢየ እግዚብሔር ዳዊት ‹‹ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ኦ ሀገረ እግዚአብሔር፤ የእግዚአብሔር ከተማ /ሀገር/ ሆይ በአንቺ የተደረገው ነገር ድንቅ ነው፡፡›› /መዝ.86፥3/ በማለት አመስግኗታል፡፡ እነዚህ በተለያየ የዘመን ርቀት ውስጥ የኖሩ የነቢዩ ዳዊትና የቅዱስ ኤፍሬም ምስጋና ምን ይደንቅ?!
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በአምላክ ሕሊና ስትታሰብ ጀምሮ በዚህ ምድር 64 ዓመት በቆየችባቸው ጊዜያትና እንደ ልጇ ባለ ትንሣኤ ተነሥታ በእግዚአብሔር ቀኝ እስካለችበት እስከ አሁን ድንቅን የምታደርግ ንግሥት፣ ድንቅ የሚደረግባት ቅድስት ናት፡፡ እመቤታችን ያደረገቻቸውን ድንቆች እጹብ ድንቅ ብሎ ከማድነቅ አልፎ ልንናገረውና ልንፈጽመው አይቻለንም፡፡ ነቢዩ ‹‹በአንቺ የተደረገው ነገር ድንቅ ነው፡፡›› እንዳለ፡፡ በእርሷ እግዚአብሔር ያደረጋቸውን ጥቂት ድንቆች እንመልከት፡-

1.    ፅንሰቷና ልደቷ ድንቅ ነው፡፡


ፅንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም በዓልን የምናዘክርበት ዕለት ነሐሴ 7 ቀን ነው፡፡ ይህ ቀን እንደምን ያለ ድንቅ ነው?! በአምላክ ሕሊና ሲታሰብ፣ በአበው ልቡና ሲመላለስ፣ በነቢያት ትንቢት ሲነገርና ለሰው ልጆች ሁሉ ምክንያተ ድህነት እንድትሆን ሲጠባበቋት የኖረች እናት በማኀጸን የተቀረጸችበት ዕለት ነበርና፡፡ የእግዚአብሔር ወዳጆች ሐናና ኢያቄም ዘር በማጣት የተነሣ ሲያዝኑና ሲያለቅሱ የኖሩባቸው ዘመናት ተገትተው መካኖች በሚለው ስም ፈንታ ወላጆች የተባሉባት ፣ አርጅተዋልና አልፎባቸዋል የተባሉባቸው ጊዜአት ተቀይረው ድንቅ ፅንስን ያገኙበት ነው፡፡ በማኀጸን ሳለች ሙት የምታነሣ፣ ሕሙማንን የምትፈውስ፣ ድውያንን የምታድን፣ እውራንን የምታበራ፣ መካኖችን ወላድ ያደረገች እናት የተገኘችበት ነውና የእመቤታችን ፅንሰቷ ድንቅ ነው፡፡

Friday, December 7, 2012

♥አባ ሊቃኖስ ዘእምተሰዓቱ ቅዱሳን♥



በስመ ሥላሴ
ወበዛቲ ዕለት አዕረፈ አባ ሊቃኖስ ዘእምተሰዓቱ ቅዱሳን
“ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅመ እግዚአብሔር”(“የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።”) መዝ.፻፲፭፡፲፭ (115፡15)
“እኛስ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ዝም ማለት አንችልም” ሐዋ.፬፡፳ (4፡20)
የቅዱሳን ሕይወት ተርታ ታሪክ ወይም ተረት አይደለም ይልቁንስ እግዚአብሔርን የሚከተሉና በሥራቸው ሁሉም የእርሱ ጥበቃ ያልተለያቸው ሰዎች ታሪክ ነው። (ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ)
 የተሰዓቱ ቅዱሳን ሐዋርያዊ ተልእኮ መቅድም
ተሰዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ የመጡት አልአሜዳ በነገሰ በአምስት ዓመት ነው።
 እንደመጡት እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነው በአክሱም ዐስራ ሁለት ዓመት ኖረዋል።
ተሰዓቱ ቅዱሳን በስም አባ አሌፍ፣ አባ አረጋዊ፣ አባ ጰንጠሌዎን፣ አባ ገሪማ፣ አባ ጵሕማ፣ አባ አፍጴ፣ አባ ሊቃኖስ፣ አባ ይምዓታ፣ አባ ጉባ ይባላሉ። እኚ አባቶች ወደ ኢትዮጵያ እንደገቡ ዝም ብሎ አልተቀመጡም፤ ለሥራቸው በር ከፋች የሆነውን ቋንቋ፣ የሕዝቡን ባህል ጠንቅቀው ካወቁ በኋላ ላይ በአንድ አከባቢ ከመኖር ይልቅ መንፈስ ቅዱስ በመደባቸው ቀጥታ ማስተማርን መርጠው መንፈሳዊ ዓላማቸውን ለማሳካት የአክሱምን ነገስታት እርዳታና ድጋፍ አልተለያቸውም ነበር። እኚው ተሰዓቱ ቅዱሳን የመጡበት ሀገራት ሮም፣ እስያ፣ አንጾኪያ፣ ቁስጥንጥንያ፣ ቂሳርያ፣ ኪልቂያ ሲሆን በነበሩበት ጊዜያትም፡-
. ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን አጽንቶልናል።
. መጽሐፍትን ተርጉሞልናል።
. ስብከተ ወንጌልን አስፋፍተዋል።
. ብዙ ገዳማትን መስርተዋል።
. ሥርዓተ ምንኩስናን አደራጅተዋል።
 ስለ እነዚህ ቅዱሳን ይህችን ታህል ካልኩኝ በዛሬው የዕረፍት በዓላቸው የሚታሰበው ከእነዚሁ ቅዱሳን አንዱ ስለሆኑ  ስለ አባ ሊቃኖስ ትንሽ ልበላችሁ።

Wednesday, December 5, 2012

ክብረ ቅዱሳን



በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
የቀበና ምስራቀ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤ/ክ የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መምህር እና የሰብከተ ወንጌል ኃላፊ
ክፍል አንድ 

ክፍል ሁለት