Thursday, October 18, 2012

†♥†"ቤተ ክርስቲያን" †♥†



"ቤተ ክርስቲያን"

ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ወገኖች፣ ለጸሎትና ለምስጋና ለስግደትና ለቁርባን የሚሰበሰቡበት ታቦትና መስቀል፣ ሥዕልና ንዋየ ቅዱሳን ያለበት የክርስቲያን ቤት ናት። ይችውም ባለሦስት ክፍል ሕንጻ ቤተክርስቲያን ስትሆን እኒህም ቅኔ ማህሌት፣ ቅድስት እና መቅደስ ናቸው።   
በክርስቶስ ያመነ ያመነች  ምእመን ምእመንት ሰውነት ቤተ ክርስቲያን (መቅደሰ እግዚአብሔር) ይባላሉ።  ጉባኤ ምዕመናን ቤተ ክርስቲያን። ቤተ ክርስቲያን ተተበብለሎ የተተረጎመው አቅሌሲያ የሚል የግሪክ ቃል ነው። “አቅሌሲያ” ማኀበር ወይም ጉባኤ ተብሎ ይተረጎማል።
“ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፎአል...” ማቴ. ፳፩፡፲፫ (21፡13)
ስለ ቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት መጽሐፍትና ቅዱሳን አባቶች በብዙ መንገድ ተርጉመውታል።
“ቤተ ክርስቲያን ወደ እግዚአብሔር እንድንቀርብ የምታደርገን የልዑል እግዚአብሔር ደጅ ናት።” (መ/ዲዲስቅሊያ)   
“የቤተ ክርስቲያን ሕይወት በመስቀል ላይ ነው፤ ስለሆነም ፈተና ይበዛባታል። ስለዚህ ከግል ሕይወታችሁ ይልቅ የቤተ ክርስቲያናችሁን አቋም አጠናክሩ።” (አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ)
“በሃይማኖት ሙቀት ቤተ ክርስቲያንን ያጋላት የመንፈስ ቅዱስ እሳት ነው።” (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)
“ለቤተ ክርስቲያን ስትል በአደባባይ  በጥፊ የተመታህ አቤቱ ይህን ማድረግህ እርሷን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው።” (ቅዱስ ያሬድ)
“ቤተ ክርስቲያን በጥምቀት አንድ የሆኑ የክርስቲያኖች የትንሳኤያቸውና የደኀነታቸው ምንጭ የክርስቶስ አካል ናት።” (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)



ምስክርነት
በአርባ ሰማንያ
በክብር አጥምቃ
በሜሮን ያተምሽኝ፣
ብታመም አክመሽ
ብራብ የመገብሽኝ፣
ባገባ አክሊል ጭነሽ
ፍጹም ያከበርሽኝ፣
ስሞት አስፈትተሽ
በመልካሙ ደጅሽ
የምታሳርፊኝ፣
ልመስክረው እንጂ
ቤተ ክርስቲያን ሆይ
ስንዱነትሽን፤
ፍጹምነትሽን።
ይህች የእግዚአብሔር ደጅ ናት፤ ወደ እርስዋ ጻድቃን ይገባሉ። መዝ. ፻፲፯፳ (117፡20)


1 comment:

  1. Way cool! Some very valid points! I appreciate you penning this post plus the
    rest of the site is extremely good.

    Take a look at my weblog ... Cheap Dr Dre Beats

    ReplyDelete