Thursday, December 20, 2012

ጥሪ - 6ኛ ፓትርያርክ ለመሾም የሚደረገውን ጊዜውን ያልጠበቀ ሩጫ ለማትደግፉ በሙሉ

  • መፈክራችን - “የቤተ ክርስቲያኔ ጉዳይ ያገባኛልየሚል ነው።
 (ደጀ ሰላም ታኅሣሥ 11/2005 .ም፤ ዲሴምበር 20/2012) በጥቂት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ፍላጎት በመዘወር ላይ ያለው 6ኛው ፓትርያርክ ምርጫ ተጠናክሮ በመቀጠል አሁንአስመራጭ ኮሚቴበማቋቋም ትልቅ ርምጃ ተስፈንጥሯል። ለዕርቅና ለሰላም ወደ አሜሪካ የላካቸውን ልዑካን መምጣት ሳይጠብቅ፣ ይዘው ለሚመጡት ምላሽ ቦታ ሳይሰጥ አዲስ ፓትርያርክ ወደ መምረጡ እየተጓዘ ነው። 
ይህንን ጉዳይ በተመለከተ በአገር ውስጥም፣ ከአገር ውጪም፣ በመላው ዓለም ያለው ኦርቶዶክሳዊ ድምጹን ማሰማት እንደሚፈልግ ይታወቃል። የአቅሙን የመፍትሔው አካል መሆን ይፈልጋል። ታዲያ ምን ይሻላልከጥቃቅን የጽዋ ማኅበራት እስከ ግዙፎቹ፣ ከማኅበረ ካህናት እስከ ማኅበረ ምዕመናን ስለ ቤተ ክርስቲያናችን እንደሚገደን መናገር የሚገባን አሁን ነው። ስለዚህም ነው ይህንን የመወያያ ርዕስ የከፈትነው። መፍትሔ የምትሏቸውን ሐሳቦች በማቅረብ፣ በየአካባቢያችሁና በየአጥቢያችሁ በአካል በመሰባሰብና በመነጋገር ለእናት ቤተ ክርስቲያናችሁ ያላችሁ አለኝታነት እንድታሳዩ ይጠበቃል። እምነት በሥራ እንጂ በምን ይገለጻል? ለመነሻ እንዲሆን ይህንን እንጠቁም። እናንተም አክሉበት።
  • መረጃውን ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን ማድረስ፣ (በስልክ የኤስ.ኤም.ኤስ መልእክቶች፣ በፌስቡክ፣ በትዊተር)
  • በየአጥቢያችን ድምጻችንን ልናሰማ የምንችልበት ስብስብ መፍጠር፣
  • ዜናውን ለመገናኛ ብዙኃን ማድረስ፣
  • ብፁዓን አባቶችን በስልክም በአካልም በመቅረብ ስለ ጉዳዩ ማነጋገር፣ በውሳኔው እንደማንስማማ ማሳወቅ፣ (አስፈላጊ ነው ብለን በምናምነው ጊዜ ስልኮቻቸውን በይፋ ለማቅረብ እንገደዳለን)
  • ጉዳያችን እና ዓላማችንድብቅ የፖለቲካ አጀንዳሳይሆን የቤተ ክርስቲያናችን አባት የመምረጥ ጉዳይ መሆኑን ለሚመለከታቸው አካላት አለ ፍርሃትና ያለ ሥጋት መግለጽ፣
  • ከመንግሥት አካላት የተደበቀ የመሥራት ፍላጎት እንደሌለን ከወዲሁ በተደጋጋሚ መግለጽ፣
  • በአገር ውስጥ ያሉ ጋዜጦችና መጽሔቶች ለጉዳዩ ሽፋን እንዲሰጡት ማበረታታት፣
  • የውጪ አገር ኢትዮጵያውያን ሚዲያዎችም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ በሚል በዚሁ ሰበብ ኢሕአዴግን ለመተቸት ሳይሆን ጉዳዩን ለክርስቲያኑ ሕዝብ በማይጎረብት መልክ እንዲያቀርቡት ማገዝ፣
  • ኦርቶዶክሳውያን ጡመራ መድረኮችም ዜናዎችን በትብብርና በኅብረት ለምእመኑ ማድረስ፣
ጨምሩበት!!!!

Tuesday, December 18, 2012

መንግሥት አቡነ ማቲያስ ዘኢየሩሳሌምን 6ኛው ፓትርያርክ ማድረግ እንደሚፈልግ ታወቀ


  • ምእመናን “ቅዱስ አባታችን” ብለው በሙሉ ልብና በፍቅር የሚታዘዙት አባት ይፈልጋሉ፤
  • ቤተ ክርስቲያን “እንቁላልና ቲማቲም የሚወረወርበት ሌላ ፓትርያርክ” አያስፈልጋትም፤
(ደጀ ሰላም ታኅሣሥ 9/2005 ዓ.ም፤ ዲሴምበር 18/2012)፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፕትርክና በ5ኛው ፓትርያርክ አረፍተ ሞት ባዶ ከሆነ ወዲህ ላለፉት 20 ዓመታት ሲያከራክር የነበረው ርዕሰ ጉዳይ እንደገና፣ እንደ አዲስ መወያያ መሆን ጀምሯል። በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃም፣ በግል ደረጃም የተለያዩ ሐሳቦችም በመንጸባረቅ ላይ ይገኛሉ። በምእመኑ ደረጃ “ነገረ ፓትርያርክ”ን ከማንሣት በፊት ዕርቀ ሰላሙ መቅደም አለበት የሚለውን አበክሮ በማቅረብ ላይ ይገኛል። የተለያዩ ደብዳቤዎችንም ለሚመለከታቸው አካላት በሙሉ አቅርበዋል። በሁሉም በኩል ሥጋት የሆነው ግን ክንደ-ፈርጣማው፣ እጀ ረዥሙ የኢሕአዴግ መንግሥት ለእምነቱ ተከታዮች ፍላጎት ሳይገዛ “የራሱን ፓትርያርክ” እንዳያስቀምጥ ነው።
በጥቅምት 6/2005 ዓ.ም ዘገባችን እንደገለጽነው በመንግሥት በኩል የመጀመሪያ የፓትርያርክ ምርጫው የምሥራቅ ሸዋ ሀገር ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አቡነ ጎርጎርዮስ ሲሆኑ ይህ ካልሆነ በሁለተኛ ደረጃ የያዛቸው በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማትያስ መሆናቸው በብዙዎች ዘንድ የታመነ ነገር ሆኗል፡፡ የቀድሞው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ለአንዳንድ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት እንደ እንደራሴያቸውም እንደተተኪያቸውም አስተዋውቀዋቸው ነበር የተባሉት የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ስድስተኛ ፓትርያርክ ይኾኑ ዘንድ መንግሥት ወስኖ መግፋት ጀምሮ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ እንደ ምንጮቻችን ማብራሪያ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ወደ ፕትርክናው መንበር መገፋታቸው÷ “የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን አቋም እና አሠራር (እነርሱ ራእይ ይሉታል) ያስቀጥላሉ፤ ለመንግሥት ለመታዘዝና ፍላጎቱን ለማስፈጸም ይመቻሉ” በሚል ሐሳብ ነው ተብሏል፡፡

Saturday, December 15, 2012

በዋልድባ ስቃዩ እና እንግልቱ ቀጥሏል

በዋልድባ ገዳም አካባቢ መንግሥት የተለያየ ሙከራዎችን እያደረገ እንደሚገኝ እና በገዳማውያኑ ላይ ስቃዩን እንደቀጠለ ይነገራል። ባለፈው ወር ላይ የገዳሙን አባቶች ጥቂት የመንግሥት ባለሥልጣናት ሰብስበው እንዳነጋገሯቸው እና ለጥር ፬ ቀን ቀጠሮ ሰጥተዋቸው እንደተበተነ ይታወሳል። በመጪው ጥር ፬ ቀን ምን ሊመጣ እንደሚችል በገዳማውያኑ ላይ ሊደርስባቸው የሚችሉትን፣ እንደ መንግሥት ባለሥልጣኖች አባባል በጥር ፬ ቀን በሚደረገው ስብሰባ ላይ የመንግሥት ተወካዮች ለገዳሙ አባቶች "ለቦታው ካሳ ተቀበሉ አለበለዚያ ሌላ ነገር ይመጣል" በማለት ገዳማውያኑን ለማስፈራራት ቢሞክሩም፥ ገዳማውያኑም "ሞትም ቢመጣ እኛ የአባቶቻችንን ርስት አሳልፈን አንሰጥም፣ እኛን ገላችሁ ሥራችሁን መስራት ትችላላችሁ" በሚል ሁኔውን እየተጠባበቁ ይገኛሉ።

በዋልድባ ስቃዩ እና እንግልቱ ቀጥሏል

 በዋልድባ ገዳም አካባቢ መንግሥት የተለያየ ሙከራዎችን እያደረገ እንደሚገኝ እና በገዳማውያኑ ላይ ስቃዩን እንደቀጠለ ይነገራል። ባለፈው ወር ላይ የገዳሙን አባቶች ጥቂት የመንግሥት ባለሥልጣናት ሰብስበው እንዳነጋገሯቸው እና ለጥር ፬ ቀን ቀጠሮ ሰጥተዋቸው እንደተበተነ ይታወሳል። በመጪው ጥር ፬ ቀን ምን ሊመጣ እንደሚችል በገዳማውያኑ ላይ ሊደርስባቸው የሚችሉትን፣ እንደ መንግሥት ባለሥልጣኖች አባባል በጥር ፬ ቀን በሚደረገው ስብሰባ ላይ የመንግሥት ተወካዮች ለገዳሙ አባቶች "ለቦታው ካሳ ተቀበሉ አለበለዚያ ሌላ ነገር ይመጣል" በማለት ገዳማውያኑን ለማስፈራራት ቢሞክሩም፥ ገዳማውያኑም "ሞትም ቢመጣ እኛ የአባቶቻችንን ርስት አሳልፈን አንሰጥም፣ እኛን ገላችሁ ሥራችሁን መስራት ትችላላችሁ" በሚል ሁኔውን እየተጠባበቁ ይገኛሉ።

Wednesday, December 12, 2012

Monday, December 10, 2012

ዕርቀ ሰላሙ በሚቀጥለው ጥር ወር በሎስ አንጀለስ በድጋሚ ይካሄዳል

 (ምንጭ:- ደጀ ሰላም )፦ ከኅዳር 26 እስከ 30 (ዲሴምበር 5-9/2012) በሰሜን አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ከተማ ሲካሄድ የሰነበተው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት ለመፍታት የተደረገው ሦስተኛ ዙር የዕርቅ ድርድር እሑድ ኅዳር 30,2005 ዓ.ም መግለጫ በማውጣት እና ለሌላ ጉባዔ ቀነ ቀጠሮ በመስጠት ተጠናቋል።
በአገር ውስጥም ሆነ በውጪ ባሉ አባቶች እና ምእመናን ዘንድ በጉጉት የሚጠበቀው የአራተኛው ፓትርያርክ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ጉዳይ ዋነኛው የመነጋገሪያ አጀንዳ በሆነበት በዚህ ጉባዔ ከሁለቱም ወገን የተለያየ ሐሳብ ከመቅረቡ አንጻር ለጊዜው ከስምምነት ላይ የተደረሰበት አይመስልም።

ከአገር ቤት የመጣው ልዑክ “ቅዱስነታቸው በመረጡት ቦታ በጸሎት ተወስነው ይቀመጡ” ሲሉ በውጪ የሚገኙት አበው ደግሞ “ከነሙሉ ማዕረጋቸው ወደ መንበራቸው ይመለሱ” የሚለውን ሐሳብ አቅርበዋል። በሁለቱም በኩል ሐሳቡ ዕልባት ሳይሰጠው ቀርቷል።


በመግባባት፣ በመከባበር እና በመደማመጥ ተደርጓል በተባለው በዚህ በአባቶች ውይይት ከቀደሙት ሁለት ጉባዔያት በተሻለ “ተስፋ ሰጪ” የአንድነት ምልክቶች የታዩበት መሆኑን ብዙዎች እየመሰከሩ ነው። ሙሉ መግለጫው በዳላስ ደ/ም/ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በምዕመናን ፊት በተነበበበት ወቅት ከሁለቱ ወገን የመጡ ልዑካን ኮፒውን በእጃቸው ይዘው ታይቷል። በዕለቱ የተነበበው መግለጫ በዋነኝነት በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ሐሳብ ሰጥቶ ያለፈ ሲሆን እኛም እንደሚከተለው ጨምቀን አቅርበነዋል።

አጆራ ተክለ ሐይማኖት

ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ በአንቺ የተደረገው ነገር ድንቅ ነው! መዝ.86፥3

በመ/ር መንግስተ አብ ፡አበጋዝ
 
የሶርያው ሊቅ ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም የምስጋና መጽሐፉ ‹‹ነቢያት ድንቅ ድንቅ ነገርን ተናገሩልሽ›› በማለት ስለ ወላዲተ አምላክ የተሰጡ ምስክርነቶች ድንቆች መሆናቸውን መስክሯል፡፡ ከዛሬ 3000 ዓመት ገደማ ቀደም ብሎም ነቢየ እግዚብሔር ዳዊት ‹‹ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ኦ ሀገረ እግዚአብሔር፤ የእግዚአብሔር ከተማ /ሀገር/ ሆይ በአንቺ የተደረገው ነገር ድንቅ ነው፡፡›› /መዝ.86፥3/ በማለት አመስግኗታል፡፡ እነዚህ በተለያየ የዘመን ርቀት ውስጥ የኖሩ የነቢዩ ዳዊትና የቅዱስ ኤፍሬም ምስጋና ምን ይደንቅ?!
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በአምላክ ሕሊና ስትታሰብ ጀምሮ በዚህ ምድር 64 ዓመት በቆየችባቸው ጊዜያትና እንደ ልጇ ባለ ትንሣኤ ተነሥታ በእግዚአብሔር ቀኝ እስካለችበት እስከ አሁን ድንቅን የምታደርግ ንግሥት፣ ድንቅ የሚደረግባት ቅድስት ናት፡፡ እመቤታችን ያደረገቻቸውን ድንቆች እጹብ ድንቅ ብሎ ከማድነቅ አልፎ ልንናገረውና ልንፈጽመው አይቻለንም፡፡ ነቢዩ ‹‹በአንቺ የተደረገው ነገር ድንቅ ነው፡፡›› እንዳለ፡፡ በእርሷ እግዚአብሔር ያደረጋቸውን ጥቂት ድንቆች እንመልከት፡-

1.    ፅንሰቷና ልደቷ ድንቅ ነው፡፡


ፅንሰታ ለእግዝእትነ ማርያም በዓልን የምናዘክርበት ዕለት ነሐሴ 7 ቀን ነው፡፡ ይህ ቀን እንደምን ያለ ድንቅ ነው?! በአምላክ ሕሊና ሲታሰብ፣ በአበው ልቡና ሲመላለስ፣ በነቢያት ትንቢት ሲነገርና ለሰው ልጆች ሁሉ ምክንያተ ድህነት እንድትሆን ሲጠባበቋት የኖረች እናት በማኀጸን የተቀረጸችበት ዕለት ነበርና፡፡ የእግዚአብሔር ወዳጆች ሐናና ኢያቄም ዘር በማጣት የተነሣ ሲያዝኑና ሲያለቅሱ የኖሩባቸው ዘመናት ተገትተው መካኖች በሚለው ስም ፈንታ ወላጆች የተባሉባት ፣ አርጅተዋልና አልፎባቸዋል የተባሉባቸው ጊዜአት ተቀይረው ድንቅ ፅንስን ያገኙበት ነው፡፡ በማኀጸን ሳለች ሙት የምታነሣ፣ ሕሙማንን የምትፈውስ፣ ድውያንን የምታድን፣ እውራንን የምታበራ፣ መካኖችን ወላድ ያደረገች እናት የተገኘችበት ነውና የእመቤታችን ፅንሰቷ ድንቅ ነው፡፡